ይመስገን ፡ ጌታ ፡ ይመስገን (Yemesgen Gieta Yemesgen)

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ

አዝ፦ ይመስገን ፡ ጌታ ፡ ይመስገን
ይመስገን ፡ ኢየሱስ ፡ ይመስገን
ይመስገን ፡ ይመስገን ፡ ይመስገን ፡ ይመስገን
ለዚህ ፡ ሁሉ ፡ ያደረሰን

እንደ ፡ ሰው ፡ ፈቃድ ፡ ቢሆን
እስከዛሬም ፡ ባልኖርን
ግን ፡ ኢየሱስ ፡ ፈቀደና
በድል ፡ ቆምን ፡ እንደገና (፪x)

አዝ፦ ይመስገን ፡ ጌታ ፡ ይመስገን
ይመስገን ፡ ኢየሱስ ፡ ይመስገን
ይመስገን ፡ ይመስገን ፡ ይመስገን ፡ ይመስገን
ለዚህ ፡ ሁሉ ፡ ያደረሰን

ጠላት ፡ መች ፡ ይህን ፡ ወዶ?
አቃተው ፡ እንጂ ፡ ተዋርዶ
ድሉ ፡ የአምላክ ፡ ሆኖበት
ያለቅሳል ፡ በእኛ ፡ መነሣት (፪x)

አዝ፦ ይመስገን ፡ ጌታ ፡ ይመስገን
ይመስገን ፡ ኢየሱስ ፡ ይመስገን
ይመስገን ፡ ይመስገን ፡ ይመስገን ፡ ይመስገን
ለዚህ ፡ ሁሉ ፡ ያደረሰን

ሞትም ፡ ቢገጥመን ፡ እኛ
ትንሣዔ ፡ አለን ፡ ዳግመኛ
ከእርሱ ፡ ፍቅር ፡ ሊለየን
ማንም ፡ አይችልም ፡ ሊያስቀረን (፪x)

አዝ፦ ይመስገን ፡ ጌታ ፡ ይመስገን
ይመስገን ፡ ኢየሱስ ፡ ይመስገን
ይመስገን ፡ ይመስገን ፡ ይመስገን ፡ ይመስገን
ለዚህ ፡ ሁሉ ፡ ያደረሰን


Xእንደ ፡ ሰው ፡ ፈቃድ ፡ ቢሆንX --> እንደ ፡ ጠላት ሃሳብ ፡ ቢሆን