የክብር ፡ መንፈስ (Yekeber Menfes)

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ

አዝ፦ የክብር ፡ መንፈስ ፡ የክብር ፡ መንፈስ
በአርያም ፡ ያለው ፡ በእግዚአብሔር ፡ መቅደስ
የክብር ፡ መንፈስ ፡ በእኛም ፡ ላይ ፡ ይፍሰስ

በእሣት ፡ ቁጥቋጦ ፡ ውስጥ ፡ ሙሴን ፡ ያናገርከው
የመላዕክትን ፡ ምግብ ፡ ለሕዝብህ ፡ ያደልከው
ስማን ፡ ጩኸታችንን ፡ እግዚአብሔር ፡ ሆይ ፡ ተነሥ
በኢትዮጵያ ፡ ምድር ፡ የድል ፡ መንፈስ ፡ አፍስስ

አዝ፦ የክብር ፡ መንፈስ ፡ የክብር ፡ መንፈስ
በአርያም ፡ ያለው ፡ በእግዚአብሔር ፡ መቅደስ
የክብር ፡ መንፈስ ፡ በእኛም ፡ ላይ ፡ ይፍሰስ

ሰለሞን ፡ መቅደሱን ፡ ሠርቶ ፡ እንደጨረሰ
በደመና ፡ ክብር ፡ ከሰማይ ፡ ፈሰሰ
ልመናችንን ፡ ስማን ፡ እግዚአብሔር ፡ ሆይ! ተነሥ
እኛን ፡ ተናገረን ፡ መንፈስህን ፡ አፍስስ

አዝ፦ የክብር ፡ መንፈስ ፡ የክብር ፡ መንፈስ
በአርያም ፡ ያለው ፡ በእግዚአብሔር ፡ መቅደስ
የክብር ፡ መንፈስ ፡ በእኛም ፡ ላይ ፡ ይፍሰስ

አጋንንቶች ፡ ይውጡ ፡ ስማቸው ፡ ይደምሰስ
ሽባዎች ፡ ይነሡ ፡ ድውዩም ፡ ይፈወስ
ጠላት ፡ ሲወድቅ ፡ እንይ ፡ በሰይፍ ፡ ሲወጋ
በጠራሃቸው ፡ ፊት ፡ የክብር ፡ እጅህን ፡ ዘርጋ

አዝ፦ የክብር ፡ መንፈስ ፡ የክብር ፡ መንፈስ
በአርያም ፡ ያለው ፡ በእግዚአብሔር ፡ መቅደስ
የክብር ፡ መንፈስ ፡ በእኛም ፡ ላይ ፡ ይፍሰስ

ስምህን ፡ እንጠራለን ፡ እግዚአብሔር ፡ ሆይ! መልስ
በጉባዔ ፡ መሃል ፡ ክብርህ ፡ ይመላለስ
ስለ ፡ ኢየሱስ ፡ ሥም ፡ ስማን ፡ ልመናችንን
በከበረው ፡ መንፈስ ፡ ጐብኛት ፡ አገራችንን

አዝ፦ የክብር ፡ መንፈስ ፡ የክብር ፡ መንፈስ
በአርያም ፡ ያለው ፡ በእግዚአብሔር ፡ መቅደስ
የክብር ፡ መንፈስ ፡ በእኛም ፡ ላይ ፡ ይፍሰስ

እንደ ፡ ቀድሞ ፡ ሕዝብህ ፡ ጌታ ፡ ስማንና
ባሪያህን ፡ አስነሣው ፡ ይስሐቅን ፡ ቀባና
ጴጥሮስ ፡ ቢሆን ፡ ጳውሎስ ፡ ሙሴ ፡ ወይ ፡ ኢያሱ
አንተ ፡ ለፈቀድከው ፡ እግዚአብሔር ፡ ቅባልን

አዝ፦ የክብር ፡ መንፈስ ፡ የክብር ፡ መንፈስ
በአርያም ፡ ያለው ፡ በእግዚአብሔር ፡ መቅደስ
የክብር ፡ መንፈስ ፡ በእኛም ፡ ላይ ፡ ይፍሰስ