From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
|
|
ሌሎች ፡ የድሮ ፡ መዝሙሮች (Other Classic Mezmur Lyrics)
|
|
የኢየሩሣሌም ፡ ልጆች ፡ ዘምሩለት
እኛም ፡ በየሥፍራችን ፡ እንደነርሱ ፡ ልንዘምር
ዘምሩ ፣ ስሙን ፡ አመስግኑ ፣ ዘምሩ ፡ ስሙን ፡ አመስግኑ ።
ሆሣዕና! ሆሣዕና! ሆሣዕና! ለዳዊት ፡ ልጅ ።
ዳዊት ፡ ንጉሥ ፡ ያለው ፡ ዕውነት ፡ ሆኖ ፡ ተገኘ
ከሕፃናት ፡ አፍ ፡ ደግሞ ፡ ምሥጋናን ፡ አዘጋጀሁ
ዘምሩ ፣ ስሙን ፡ አመስግኑ ፣ ዘምሩ ፡ ስሙን ፡ አመስግኑ ።
ሆሣዕና! ሆሣዕና! ሆሣዕና! ለዳዊት ፡ ልጅ ።
አምላክ ፡ አባታችን ፡ ነው ፡ መንገዱንም ፡ ሊመራን
ቅዱስ ፡ ቃሉ ፡ ሰጠነ ፡ ምሥጋናችን ፡ እናቅርብ
ዘምሩ ፣ ስሙን ፡ አመስግኑ ፣ ዘምሩ ፡ ስሙን ፡ አመስግኑ ።
ሆሣዕና! ሆሣዕና! ሆሣዕና! ለዳዊት ፡ ልጅ ።
ፍጥረት ፡ ሁሉ ፡ ተነሡ ፡ ዘምሩለት ፡ ባንድነት
እስከ ፡ ሰማይ ፡ እንዲደርስ ፡ ድምፃችሁን ፡ ከፍ ፡ አድርጉ
ዘምሩ ፣ ስሙን ፡ አመስግኑ ፣ ዘምሩ ፡ ስሙን ፡ አመስግኑ ።
ሆሣዕና! ሆሣዕና! ሆሣዕና! ለዳዊት ፡ ልጅ ።
|