From WikiMezmur: Mezmur Lyrics
|
|
ሌሎች ፡ የድሮ ፡ መዝሙሮች (Other Classic Mezmur Lyrics)
|
|
አዝ፦ ለውጠኝ (፬x) ፡ ጌታዬ
አንተን ፡ እንድትመስል ፡ አድርጋት
ኢየሱስ ፡ ሆይ ፡ ሕይወቴን
እስከ ፡ መቼ ፡ ልኑር ፡ ጌታ ፡ በዚህ ፡ ሕይወት?
አንተን ፡ በማሳዘን ፡ ቁስልህን ፡ በመውጋት
መኖር ፡ አልፈልግም ፡ እያሳዘንኩ ፡ አንተን
መለወጥ ፡ እሻለሁ ፡ ፍፁም ፡ መቀየርን
አዝ፦ ለውጠኝ (፬x) ፡ ጌታዬ
አንተን ፡ እንድትመስል ፡ አድርጋት
ኢየሱስ ፡ ሆይ ፡ ሕይወቴን
ሕይወቴ ፡ ይታደስ ፡ ይለወጥ ፡ ይቀየር
እኔነቴን ፡ ትቶ ፡ ክብርህን ፡ ይመስክር
ልቤ ፡ ይታዘዝህ ፡ ይንቀጥቀጥልህ
በፊትህም ፡ ይቅለጥ ፡ ይንበርከክልህ
አዝ፦ ለውጠኝ (፬x) ፡ ጌታዬ
አንተን ፡ እንድትመስል ፡ አድርጋት
ኢየሱስ ፡ ሆይ ፡ ሕይወቴን
መንፈስህ ፡ ይማርከው ፡ ሕይወቴን ፡ ይረከብ
የዓለምን ፡ ነገር ፡ ፍፁም ፡ እንዳያስብ
ሁልጊዜ ፡ ወዳንተ ፡ ጥማት ፡ እንዲኖረኝ
ጌታ ፡ ኢየሱስ ፡ ሆይ ፡ ለውጠኝ ፡ ለውጠኝ
አዝ፦ ለውጠኝ (፬x) ፡ ጌታዬ
አንተን ፡ እንድትመስል ፡ አድርጋት
ኢየሱስ ፡ ሆይ ፡ ሕይወቴን
ብዙ ፡ ጊዜ ፡ ተጓዝኩ ፡ ክርስቲያን ፡ በመምሰል
ዕድሜዬን ፡ ገፋሁ ፡ ራሴን ፡ በማታለል
ዛሬ ፡ ግን ፡ በቅቶኛል ፡ አስመስሎ ፡ መኖር
አሁን ፡ ተለውጬ ፡ ልኑር ፡ ለአንተ ፡ ክብር
አዝ፦ ለውጠኝ (፬x) ፡ ጌታዬ
አንተን ፡ እንድትመስል ፡ አድርጋት
ኢየሱስ ፡ ሆይ ፡ ሕይወቴን
|