ከፍ ፡ በል ፡ ከሁለም ፡ በላይ (Kef Bel Kehulum Belay)

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ

አየሁ ፡ ጌታዬ ፡ ምስኪኑን ፡ ሲረዳ
አየሁ ፡ ጌትዬ ፡ ሲደርስ ፡ ለተጐዳ
ጌታንማ ፡ በእውነትማ ፡ ለሚጠሩት
የቅርብ ፡ እንጂ ፡ አይደለም ፡ የሩቅ

አዝ፦ ከፍ ፡ በል ፡ ከሁሉም ፡ በላይ
ከፍ ፡ በል ፡ ከሁሉም ፡ በላይ (፪x)
ደስታዬ ፡ ስትከብር ፡ ሳይ
እርካታዬ ፡ ስትከብር ፡ ሳይ (፪x)

በጉባኤ ፡ መኻል ፡ ስትከብር ፡ እያየሁ
እንዳት ፡ ችዬ ፡ ዝም ፡ እላለሁ (፪x)
ሕዝብህ ፡ ሲያደንቅህ ፡ እያየሁ
እንዴት ፡ ችዬ ፡ ዜም ፡ እላለሁ (፪x)
መቃብር ፡ ተከፍቶ ፡ እያየሁ
እንዳት ፡ ችዬ ፡ ዝም ፡ እላለሁ (፪x)
ደያቢሎስ ፡ ሲረገጥ ፡ እያየሁ
እንዴት ፡ ችዬ ፡ ዝም ፡ እላለሁ (፪x)

ጌታ ፡ ጌታ ፡ ነህ ፡ ይላሉ
አዳኝ ፡ ይላሉ
ንጉሥ ፡ ነህ ፡ ይላሉ

እኔ ፡ እንደማውቀው ፡ ከሁሉ ፡ በላይ ፡ ነህ (፬x)
እኔም ፡ ልናገር ፡ ከሁሉ ፡ በላይ ፡ ነህ (፬x)
እኔም ፡ እላለሁ ፡ ከሁሉ ፡ በላይ ፡ ነህ (፬x)

አንተ ፡ ለእኔ ፡ መልካም ፡ ነህ ፡ ለእኔ ፡ ለእኔ (፬x)
ለእኔ ፡ መልካም ፡ ነህ ፡ ለእኔ ፡ ለእኔ (፬x)
ለእኔ ፡ መልካም ፡ ነህ ፡ ለእኔ ፡ ለእኔ (፬x)