ክበር ፡ በሉት ፡ እርሱን (Keber Keber Belut Ersun)

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ

አዝክበር ፡ ክበር ፡ ክበር ፡ በሉት ፡ እርሱን (፪x)
ኢየሱስ ፡ ከፍ ፡ ሲል ፡ ያፈሳል ፡ መንፈሱን

ጌታ ፡ ኢየሱስ ፡ ብሎ ፡ ጠርቶ ፡ ተማጽኖታል
ከተላት ፡ ጉያ ፡ ስር ፡ ወስዶ ፡ ቀብቶታል
በማዳኑ ፡ ጥላ ፡ ጋርዶ ፡ አበጃጅቶታል
ለእግዚአብሔር ፡ ክብር ፡ ተናገር ፡ ብሎታል

አዝክበር ፡ ክበር ፡ ክበር ፡ በሉት ፡ እርሱን (፪x)
ኢየሱስ ፡ ከፍ ፡ ሲል ፡ ያፈሳል ፡ መንፈሱን

ሕያዋን ፡ ልጆቹ ፡ ክብርን ፡ እየሰጡ
በማዳኑ ፡ ጥላ ፡ ገብተው ፡ ተሸጐጡ
ኢየሱስ ፡ ኢየሱስ ፡ ብለው ፡ ሲዘምሩ
እየሰፋ ፡ ሄደ ፡ የወንጌል ፡ ድንበሩ

አዝክበር ፡ ክበር ፡ ክበር ፡ በሉት ፡ እርሱን (፪x)
ኢየሱስ ፡ ከፍ ፡ ሲል ፡ ያፈሳል ፡ መንፈሱን

አባታቸው ፡ ከብሮአል ፡ በእነርሱ ፡ ምሥጋና
ሁላችሁ ፡ ተነሱ ፡ ይደርደር ፡ በገና
እስትንፋስ ፡ ያላችሁ ፡ ስገዱ ፡ አሜን ፡ በሉ
ኢየሱስ ፡ ሲነግስ ፡ የእኛ ፡ ነው ፡ ድሉ

አዝክበር ፡ ክበር ፡ ክበር ፡ በሉት ፡ እርሱን (፪x)
ኢየሱስ ፡ ከፍ ፡ ሲል ፡ ያፈሳል ፡ መንፈሱን

እጆች ፡ ያጨብጭቡ ፡ ምላስም ፡ ይዘምር
የዳነ ፡ ህዝብ ፡ ሁሉ ፡ ይምጣ ፡ ለእርሱ ፡ ክብር
በደመቀ ፡ ዕልልታ ፡ አምላካችን ፡ ይንገሥ
ለማየት ፡ እንድንችል ፡ በረከቱን ፡ ሲያፈስ

አዝክበር ፡ ክበር ፡ ክበር ፡ በሉት ፡ እርሱን (፪x)
ኢየሱስ ፡ ከፍ ፡ ሲል ፡ ያፈሳል ፡ መንፈሱን