ጌታችንን ፡ አመስግኑት (Gietachenen Amesgenut)

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ

ጌታችን ፡ አመስግኑት ፡ በደስታ ፡ ዝማሬ
ሕጻናት ፡ ያመስግኑት ፡ ኢየሱስ ፡ ጌታችንን
ታናሾችን ፡ ወደደ ፡ ወደርሱም ፡ ጠራቸው
በክንዱም ፡ አቀፋቸው ፡ ነፍሱንም ፡ ሰጣቸው

ጐልማሶች ፡ ያመስግኑህ ፡ ቅኔም ፡ ይቀኙልህ
ንጹህ ፡ ያለ ፡ ኃጢአት ፡ በምድር ፡ የነበርህ
መታዘዝ ፡ አስተምረን ፡ ክፉን ፡ እንድንሸሽ
በሰማያዊ ፡ መቅደስ ፡ ከአንተ ፡ ጋር ፡ እንድንሆን

ሴቶችም ፡ ያመስግኑህ ፡ አንተ ፡ የድንግል ፡ ልጅ
ፀጋና ፡ ትህትና ፡ ሕይወትን ፡ የተሞላህ
ፀጋህን ፡ አልብሳቸው ፡ ሰላምህን ፡ ስጣቸው
በፊትህ ፡ የሚያበራ ፡ እምነት ፡ ላክላቸው

በአንድነት ፡ ተባብረን ፡ ለአንተ ፡ እንቀኝልህ
ብርሃን ፡ መሪ ፡ ሁንልን ፡ በልጅነታችን
ወደ ፡ ላይም ፡ ምራነ ፡ በምድር ፡ ላይ ፡ ሳለን
እንዳንተ ፡ እንድንሆን ፡ በጥበብህ ፡ አድገን