ጋሻ ፡ ጦርህን ፡ አንሣ (Gasha Torehen Ansa)

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ

አዝ፦ ጋሻ ፡ ጦርህን ፡ አንሣ ፡ እግዚአብሔር
የዲያብሎስን ፡ ምሽግ ፡ አፈራርስ ፡ ምሽጉን ፡ አፈራርስ
ቀስቱን ፡ ስበርልን ፡ ፍላፃውን ፡ መልስ
በታላቅ ፡ ስምህን ፡ የዲያብሎስን ፡ ሰፈር ፡ ይተራመስ

1. ጦርን ፡ አስከስቶ ፡ የከበበንን
በቀኝ ፡ በግራ ፡ የወረሩንን
የሚያውከንን ፡ የዲያብሎስ ፡ መንጋ
በታላቅ ፡ ስምህ ፡ በጦርህ ፡ ይወጋ

አዝ፦ ጋሻ ፡ ጦርህን ፡ አንሣ ፡ እግዚአብሔር
የዲያብሎስን ፡ ምሽግ ፡ አፈራርስ ፡ ምሽጉን ፡ አፈራርስ
ቀስቱን ፡ ስበርልን ፡ ፍላፃውን ፡ መልስ
በታላቅ ፡ ስምህን ፡ የዲያብሎስን ፡ ሰፈር ፡ ይተራመስ

2. በነጐድጓድ ፡ ውረድ ፡ በኃይልህ ፡ ተነሣ
የአጋንንትን ፡ ሠፈር ፡ አሳጣው ፡ መድረሻ
በደምህ ፡ የተዋጀውን ፡ ሕዝብህን ፡ የሚያውኩ
በኢየሱስ ፡ ደም ፡ በስሙ ፡ ይድቀቁ

አዝ፦ ጋሻ ፡ ጦርህን ፡ አንሣ ፡ እግዚአብሔር
የዲያብሎስን ፡ ምሽግ ፡ አፈራርስ ፡ ምሽጉን ፡ አፈራርስ
ቀስቱን ፡ ስበርልን ፡ ፍላፃውን ፡ መልስ
በታላቅ ፡ ስምህን ፡ የዲያብሎስን ፡ ሰፈር ፡ ይተራመስ

3. በግርማህ ፡ በክብርህ ፡ በኃይልህ ፡ ውረድ
ምድር ፡ ትገዛልህ ፡ ተራራም ፡ ይናድ
ና ፡ አግዘን ፡ ጌታ ፡ ጠላት ፡ ይደናገጥ
በመስቀሉ ፡ ኃይል : ዲያብሎስ ፡ ይረገጥ

አዝ፦ ጋሻ ፡ ጦርህን ፡ አንሣ ፡ እግዚአብሔር
የዲያብሎስን ፡ ምሽግ ፡ አፈራርስ ፡ ምሽጉን ፡ አፈራርስ
ቀስቱን ፡ ስበርልን ፡ ፍላፃውን ፡ መልስ
በታላቅ ፡ ስምህን ፡ የዲያብሎስን ፡ ሰፈር ፡ ይተራመስ

4. የወንጌል ፡ እውነት ፡ የሚከላልስ
ሕዝቡን ፡ የሚለያይ ፡ የክፉ ፡ መንፈስ
በምድርም ፡ የዘራውም ፡ የጨለማ ፡ ሥራ
በመስቀሉ ፡ ኃይል ፡ ይብነን ፡ እንዳቧራ