ኢየሱስን ፡ ማገልገል (Eyesusen Magelgel)

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ

ኢየሱስን ፡ ማገልገል ፡ ዋጋ ፡ ይሰጣል
ፍፁም ፡ ደስታ ፡ ከእርሱ ፡ ይገኛል
በቃሉ ፡ መታመን ፡ ታላቅ ፡ እረፍት ፡ ነው

አዝ፦ ስለዚህ ፡ ና ፡ አገልግለው
ኢየሱስን ፡ አገልግል
እድሜህን ፡ ሁሉ
ዋጋ ፡ ታገኛለህና
በመንገድህ ፡ እንኳ
ችግር ፡ ቢያገኝህ
እርሱ ፡ ጋሻ ፡ ይሆንልሃል

ኢየሱስን ፡ አገልግል
የሆነ ፡ ቢሆን ፡ በሥራህ ፡ ሁሉ
ታማኝ ፡ ሁነህ ፡ ቁም ፡ በቃሉ
መታመን ፡ ታላቅ ፡ ሀብት ፡ አለው

አዝ፦ ስለዚህ ፡ ና ፡ አገልግለው
ኢየሱስን ፡ አገልግል
እድሜህን ፡ ሁሉ
ዋጋ ፡ ታገኛለህና
በመንገድህ ፡ እንኳ
ችግር ፡ ቢያገኝህ
እርሱ ፡ ጋሻ ፡ ይሆንልሃል

ምናልባት ፡ ጨለማ ፡ ይሆንብናል
የሚፈትነን ፡ ኃዘን ፡ ይመጣል
ክቡር ፡ አዳኛችን
ጠባቂያችን ፡ ነው

አዝ፦ ስለዚህ ፡ ና ፡ አገልግለው
ኢየሱስን ፡ አገልግል
እድሜህን ፡ ሁሉ
ዋጋ ፡ ታገኛለህና
በመንገድህ ፡ እንኳ
ችግር ፡ ቢያገኝህ
እርሱ ፡ ጋሻ ፡ ይሆንልሃል