እግዚአብሔር ፡ ይመስገን ፡ እላለሁኝ (Egziabhier Yemesgen Elalehugn)

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ

አዝ፦ እግዚአብሔር ፡ ይመስገን ፡ እላለሁኝ
እኔ ፡ ማዳኑን ፡ ስላየሁኝ

በበረሃ ፡ ስጓዝ ፡ ሲደርስብኝ ፡ ጉዳት
ረሃብና ፡ ጥማት ፡ ሕይወቴን ፡ ሲይዛት
ማነው ፡ ያዘነልኝ ፡ ወድቄ ፡ እንዳልቀር?
የደገፈኝ ፡ ማነው ፡ እንዳልሰባበር?

አዝ፦ እግዚአብሔር ፡ ይመስገን ፡ እላለሁኝ
እኔ ፡ ማዳኑን ፡ ስላየሁኝ

በመከራ ፡ ሥቃይ ፡ ነፍሴ ፡ ስትጨነቅ
ልቤ ፡ በፍርሃት ፡ በሃዘን ፡ ሲጥለቀለቅ
በድካም ፡ ተይዤ ፡ ወጀብ ፡ ሲያንገላታኝ
በቃልህ ፡ ታምኜ ፡ እንድቆም ፡ አደረግኸኝ

አዝ፦ እግዚአብሔር ፡ ይመስገን ፡ እላለሁኝ
እኔ ፡ ማዳኑን ፡ ስላየሁኝ

ጠልቀው ፡ በማያውቁት ፡ ውስጣዊ ፡ ሕይወቴን
ሲያወጉ ፡ እየሰማሁ ፡ የእኔን ፡ ከንቱነቴን
በዚህ ፡ ሁሉ ፡ መንገድ ፡ ለእኔ ፡ ድልን ፡ ሰጠኸኝ
ደካማ ፡ ምስኪኑን ፡ ለክብርህ ፡ አቆምኸኝ

አዝ፦ እግዚአብሔር ፡ ይመስገን ፡ እላለሁኝ
እኔ ፡ ማዳኑን ፡ ስላየሁኝ