ቸር ፡ ነህ (Cher Neh)

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ

አዝ፦ ቸር ፡ ነህ ፡ ጌታዬ ፡ ቸር ፡ ነህ
ቸር ፡ ነህ ፡ ለእኔስ ፡ ቸር ፡ ነህ

1. በቀራንዮ ፡ መስቀል ፡ ላይ
ስራዬን ፡ አንተ ፡ ሰርተኻል
ቀንበሬን ፡ አንተ ፡ ሰበርከው
እዳዬን ፡ ከእኔ ፡ አስወገድከው (፪x)

አዝ፦ ብዙ ፡ ብዙ ፡ ነው ፡ ቸርነትህ ፡ ብዙ ፡ ነው
ብዙ ፡ ብዙ ፡ ነው ፡ በጐነትህ ፡ ብዙ ፡ ነው (፪x)
ቸር ፡ ነህ ፡ ጌታዬ ፡ ቸር ፡ ነህ
ቸር ፡ ነህ ፡ ለኔስ ፡ ቸር ፡ ነህ

2. በደሙ ፡ አጥቦ ፡ አንፅቶ
ሕይወቴንም ፡ ቀድሶ
ሰው ፡ አደረገን ፡ ረድኤቴ
እኔም ፡ ላክብረው ፡ ከልቤ (፪x)

አዝ፦ ብዙ ፡ ብዙ ፡ ነው ፡ ቸርነትህ ፡ ብዙ ፡ ነው
ብዙ ፡ ብዙ ፡ ነው ፡ በጐነትህ ፡ ብዙ ፡ ነው (፪x)
ቸር ፡ ነህ ፡ ጌታዬ ፡ ቸር ፡ ነህ
ቸር ፡ ነህ ፡ ለኔስ ፡ ቸር ፡ ነህ

3. ለእኔ ፡ እንዳንተ ፡ ማን ፡ አለኝ
የውስጥ ፡ የልቤን ፡ የሚረዳልኝ
ስለ ፡ እኔ ፡ ሁሉ ፡ ታስባለህ
በአብ ፡ ቀኝ ፡ ትማልዳለህ (፪x)

አዝ፦ ብዙ ፡ ብዙ ፡ ነው ፡ ቸርነትህ ፡ ብዙ ፡ ነው
ብዙ ፡ ብዙ ፡ ነው ፡ በጐነትህ ፡ ብዙ ፡ ነው (፪x)
ቸር ፡ ነህ ፡ ጌታዬ ፡ ቸር ፡ ነህ
ቸር ፡ ነህ ፡ ለኔስ ፡ ቸር ፡ ነህ