በበረሃ ፡ ስጓዝ ፡ ጉዳት ፡ ቢደርስብኝ (Bebereha Sguaz Gudat Bidersibigne)

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ

እግዚአብሔር ፡ ይመስገን ፡ እላለሁኝ
እኔ ፡ ማዳኑን ፡ ስላየሁኝ

በበረሃ ፡ ስጓዝ ፡ ቢደርስብኝ ፡ ጉዳት
ረሃብና ፡ ጥማት ፡ ሕይወቴን ፡ ሲይዛት
ማነው ፡ ያዘነልኝ? ወድቄ ፡ እንዳልቀር
የደገፈኝ ፡ ማነው ፡ እንዳልሰባበር?

እግዚአብሔር ፡ ይመስገን ፡ እላለሁኝ
እኔ ፡ ማዳኑን ፡ ስላየሁኝ

በመከራ ፡ ሥቃይ ፡ ነፍሴ ፡ ስትጨነቅ
ልቤ ፡ በፍርሃት ፡ በሃዘን ፡ ሲጥለቀለቅ
በድካም ፡ ተይዤ ፡ ወጀብ ፡ ሲያንገላታኝ
በቃልህ ፡ ታምኜ ፡ እንድቆም ፡ አረግኸኝ

እግዚአብሔር ፡ ይመስገን ፡ እላለሁኝ
እኔ ፡ ማዳኑን ፡ ስላየሁኝ

ጠልቀው ፡ በማያውቁት ፡ ውስጣዊ ፡ ሕይወቴን
ሲያወጉ ፡ እየሰማሁ ፡ የእኔን ፡ ከንቱነቴን
በዚህ ፡ ሁሉ ፡ መንገድ ፡ ለእኔ ፡ ድልን ፡ሰጠኸኝ
ደካማ ፡ ምስኪኑን ፡ ለክብርህ ፡ አቆምኸኝ

እግዚአብሔር ፡ ይመስገን ፡ እላለሁኝ
እኔ ፡ ማዳኑን ፡ ስላየሁኝ