From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
|
|
ሌሎች ፡ የድሮ ፡ መዝሙሮች (Other Classic Mezmur Lyrics)
|
|
በዓለሙ ፡ እንደ ፡ ቤቴ
የለም ፡ የከበረ ፡ ለእኔ
የሚወደው ፡ ልቤ
ጐጆ ፡ ሆኖ ፡ ምንም ፡ እንኳ
ጌጥና ፡ ውበት ፡ ቢያጣ
ከንጉሥ ፡ አዳራሽ ፡ ቤቴ
ክቡር ፡ ሆነ ፡ ለእኔ
የወደዱኝ ፡ ወላጆቼ
ከታናሽነቴ ፡ ጊዜ
ይዘው ፡ ጣሩ ፡ ለእኔ
ሥራቸው ፡ ቤትን ፡ አቆመ
ፍቅራቸውም ፡ ያን ፡ አሞቀ
ፍቅር ፡ ሰላም ፡ የኖረበት
አልረሳም ፡ ያንን ፡ ቤት
ቤቴ ፡ በሁሉ ፡ መከራ
ይሆነኛል ፡ መጠጊያ
በችጋርም ፡ አምባ
የሌላ ፡ ቤት ፡ ሲዘጋብኝ
አንድ ፡ ቤት ፡ ተከፍቶ ፡ ሊቆየኝ
እንደ ፡ እናቴ ፡ ልብ ፡ ቤትም
በዓለም ፡ አይገኝም
በዚያ ፡ ቁስል ፡ ይጠጋል
እንባ ፡ ከዓይን ፡ ይታበሳል
ልቤ ፡ ይጸናናል
ትዕግሥት ፡ ለስንፍናዬ
ሥርየት ፡ ለሁሉ ፡ በደሌ
በጭንቀት ፡ ይገኛል ፡ ረድዔት
በወላጆቼ ፡ ቤት
ያ ፡ ቤት ፡ ግን ፡ ወድሞ ፡ ሊቀር
ወላጆች ፡ ለቀው ፡ ከምድር
ሲገቡ ፡ መቃብር
በአምላክ ፡ ቤት ፡ ግን ፡ ሳይለዩ
ልጆቹ ፡ ሊተባበሩ
ፍቅር ፡ ደስታ ፡ በመላበት
በሰማያዊ ፡ ቤት
|