አሜን ፡ ክበር ፡ ጸሎታችን ፡ ተሰምቷል (Amen Kiber Tselotachin Tesemtoal)

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ

አዝ ፣
አሜን ፣ ክበር ፣
ጸሎታችን ፡ ተሰምቷል
ጠላት ፡ ቅሥሙ ፡ ተሰብሯል
በአዲስ ፡ ኃይል ፣ በፍቅር ፣
ጉዞ ፡ ጀምረናል ።

አሜን ፣ ክበር ፣ ጌታ ፡ ስምህ ፡ ይባረክ
ለእኛ ፡ ኃጢአተኞች ፡ ኃይልህን ፡ ገለጽክ
ጸሎታችንን ፡ ሰማህ ፣ አዲስ ፡ ኃይል ፡ ሰጠኸን
በጠላታችን ፡ ፊት ፡ ከፍ ፡ ከፍ ፡ አደረግኸን

አዝ ፣
አሜን ፣ ክበር ፣
ጸሎታችን ፡ ተሰምቷል
ጠላት ፡ ቅሥሙ ፡ ተሰብሯል
በአዲስ ፡ ኃይል ፣ በፍቅር ፣
ጉዞ ፡ ጀምረናል ።

ጩኸታችንን ፡ ሰምቷል ፣ ጌታ ፡ ፈውሶናል
ፍቅሩን ፡ አጐናጽፎ ፡ በድል ፡ አቁሞናል
መች ፡ አየኸንና ፡ እንደ ፡ በደላችን
በትዕግሥት ፡ እያየህ ፡ ያን ፡ ክፉ ፡ ሥራችን

አዝ ፣
አሜን ፣ ክበር ፣
ጸሎታችን ፡ ተሰምቷል
ጠላት ፡ ቅሥሙ ፡ ተሰብሯል
በአዲስ ፡ ኃይል ፣ በፍቅር ፣
ጉዞ ፡ ጀምረናል ።

እኛን ፡ የገረመን ፡ የጌታ ፡ ፍቅር ፡ ነው
በርከክ ፡ ስንል ፡ ጭራሽ ፡ ፀሎትን ፡ ሲሰማው
ትዕግሥተኛው ፡ ጌታ ፡ ፍቅር ፡ ያስገደደው
ያዝንልናል ፡ እኮ ፡ ድካማችን ፡ ሲያየው

አዝ ፣
አሜን ፣ ክበር ፣
ጸሎታችን ፡ ተሰምቷል
ጠላት ፡ ቅሥሙ ፡ ተሰብሯል
በአዲስ ፡ ኃይል ፣ በፍቅር ፣
ጉዞ ፡ ጀምረናል ።

ጠላትም ፡ ቢከሰን ፡ ከአንተ ፡ ሊለየን
እግዚአብሔር ፡ ተመስገን ፣ ቅስሙን ፡ ሰበርክልን
ይህ ፡ እኛን ፡ ሲገርመን ፡ አዲስ ፡ ኃይል ፡ ሰጠኸን
የጠላት ፡ ድል ፡ መምቻ ፡ ኃይል ፡ አጐናጸፍኸን ።

አዝ ፣
አሜን ፣ ክበር ፣
ጸሎታችን ፡ ተሰምቷል
ጠላት ፡ ቅሥሙ ፡ ተሰብሯል
በአዲስ ፡ ኃይል ፣ በፍቅር ፣
ጉዞ ፡ ጀምረናል ።