ምሥጋና (Mesgana) - ቴዎድሮስ ፡ ታደሰ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ቴዎድሮስ ፡ ታደሰ
(Teodros Tadesse)

Teodros Tadesse 2.jpg


(2)

የካሳ ፡ ዘመን
(Yekasa Zemen)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፬ (2012)
ቁጥር (Track):

፲ ፩ (11)

ርዝመት (Len.): 4:25
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የቴዎድሮስ ፡ ታደሰ ፡ አልበሞች
(Albums by Teodros Tadesse)

ፈረሱንና ፡ ፈረሰኛውን
በባሕር ፡ የጣለ ፡ እኛን ፡ አሻግሮን
በሚያስፈራ ፡ ግርማው ፡ ከፊት ፡ እየመራ
ነጥቆ ፡ ያስመለጠን ፡ ከዚያ ፡ ባለጋራ (፪x)

አዝትላንት ፡ የረዳን ፡ ያገዘን ፡ ጌታ
ዛሬም ፡ በዙፋኑ ፡ አለና ፡ እንጨምር ፡ ምሥጋና (፪x)
ብዙ ፡ ብዙ (ምሥጋና)
ከልባችን (ምሥጋና)
እንሰዋ (ምሥጋና)
ለጌታችን (ምሥጋና) (፪x)

ሌሊት ፡ በእሳት ፡ አምድ ፡ ቀኑን ፡ በደመና
እስራኤልን ፡ የሚጠብቅ ፡ ለአፍታ ፡ ደክሞ ፡ አያውቅም
መንገድ ፡ አስጀምሮ ፡ ጥሎ ፡ የማይጠፋ
የማይሻር ፡ ኪዳን ፡ አለው ፡ ጽኑ ፡ ፍቅር ፡ ቀን ፡ ቢከፋ

እንደኃያልና ፡ እንደጨካኝ ፡ ወጥቶ
በሰልፉ ፡ ሜዳ ፡ ላይ ፡ ውጊያውን ፡ ተዋግቶ
ድል ፡ አድርጐ ፡ ባለድል ፡ ያደረገን ፡ እርሱ ፡ ነው
ይክበር ፡ ይንገሥልን ፡ ወደን ፡ እናምልከው ፡ ፈቅደን ፡ እናምልከው

አዝትላንት ፡ የረዳን ፡ ያገዘን ፡ ጌታ
ዛሬም ፡ በዙፋኑ ፡ አለና ፡ እንጨምር ፡ ምሥጋና (፪x)
ብዙ ፡ ብዙ (ምሥጋና)
ከልባችን (ምሥጋና)
እንሰዋ (ምሥጋና)
ለጌታችን (ምሥጋና) (፪x)

ሌሊት ፡ በእሳት ፡ አምድ ፡ ቀኑን ፡ በደመና
እስራኤልን ፡ የሚጠብቅ ፡ ለአፍታ ፡ ደክሞ ፡ አያውቅም
መንገድ ፡ አስጀምሮ ፡ ጥሎ ፡ የማይጠፋ
የማይሻር ፡ ኪዳን ፡ አለው ፡ ጽኑ ፡ ፍቅር ፡ ቀን ፡ ቢከፋ

ብዙ ፡ ብዙ (ምሥጋና)
ከልባችን (ምሥጋና)
እንሰዋ (ምሥጋና)
ለጌታችን (ምሥጋና) (፪x)