Teodros Tadesse/Yemot Awaj

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ

የሞት አዋጅ አይሠራም በሕይወቴ
አይሆንም በሕይወቴ
ገልብጦታል ነገሩን/እየሱስ አባቴ (፪x)

የሚውጠውን ፈልጎ እንደሚያገሣ አምበሳ
ዙሪያ ዙሪያዬን ቢያንዣብብ ሰላሜን ደርሶ ሊነሳ
መጣ ከሰማይ ወረደ ነደደ የአምላኬ ቁጣ
በሳት ቅጥሩ ቀጠረኝ ጠላት በበቀል ሳይወጣ

ስልጣን የለውም በኔ ላይ
አለቃ አይሆንም የበላይ
እንዲያው አይደለም መጓደዴ
በመስቀል ሞት ነው መወለዴ (፬x)

የሞት አዋጅ አይሠራም በሕይወቴ
አይሆንም በሕይወቴ
ገልብጦታል ነገሩን/እየሱስ አባቴ (፪x)

የስንቱን ጀግና ቤት ደፍሮ መቅሰፍቱን ይዞ ሲገባ
አሳየኝ ገና ከሩቁ አጥፊውን ገዳዩን ሌባ
ሸንጎ ሰብስቦ ሲመክር ታሪኬን መና ሊያደርገው
ምልክት ሰጦ አስመለጠኝ እኔ ማመልከው እንዲህ ነው

ስልጣን የለውም በኔ ላይ
አለቃ አይሆንም የበላይ
እንዲያው አይደለም መጓደዴ
በመስቀል ሞት ነው መወለዴ (፬x)

የሞት አዋጅ አይሠራም በሕይወቴ
አይሆንም በሕይወቴ
ገልብጦታል ነገሩን/ኢየሱስ አባቴ (፪x)

Watch on YouTube