መቼ ፡ ተወኝ (Mech Tewegn) - ቴዎድሮስ ፡ ታደሰ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ቴዎድሮስ ፡ ታደሰ
(Teodros Tadesse)

Teodros Tadesse 1.jpeg


(1)

አያምረኝም
(Ayamregnm)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፩ (2009)
ቁጥር (Track):

(8)


ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የቴዎድሮስ ፡ ታደሰ ፡ አልበሞች
(Albums by Teodros Tadesse)

 
አዝ፦ መራመድ ፡ ሲያቅተኝ ፡ በጽድቅ ፡ ጐዳና
ነፍሴም ፡ ስትጨነቅ ፡ በኀጢአት ፡ ፈተና
ሥጋዬም ፡ ሲረክስ ፡ ጠፍቶ ፡ ህሊናዬ
እንደሰው ፡ መች ፡ ተወኝ (፪x) ፡ ጌታዬ
ጨክኖ ፡ መች ፡ ተወኝ (፪x) ፡ ጌታዬ

መጠቋቆሚያ ፡ ሲያደርገኝ ፡ ሰው ፡ ሁሉ
እንግዲህ ፡ ተስፋም ፡ የለው ፡ እያሉ
መች ፡ ቀረሁ ፡ ወድቄ ፡ ተሸማቅቄ
ከአምላኬ ፡ ጉያ ፡ እንዲያው ፡ ርቄ
እንደገና ፡ አረገኝ ፡ ቀና
እንደገና ፡ አረገኝ ፡ ቀና
(፪x)

አዝ፦ መራመድ ፡ ሲያቅተኝ ፡ በጽድቅ ፡ ጐዳና
ነፍሴም ፡ ስትጨነቅ ፡ በኀጢአት ፡ ፈተና
ሥጋዬም ፡ ሲረክስ ፡ ጠፍቶ ፡ ህሊናዬ
እንደሰው ፡ መች ፡ ተወኝ (፪x) ፡ ጌታዬ
ጨክኖ ፡ መች ፡ ተወኝ (፪x) ፡ ጌታዬ

ምህረትህን ፡ የለመደ ፡ አመለኛ
ተው ፡ ቢሉን ፡ የማይሰማ ፡ እልከኛ
ብለው ፡ ፈረዱ ፡ በእግዚአብሔር ፡ ፍቅር
በቸርነቱ ፡ ብዙ ፡ የተረዱ
የራሳቸውን ፡ ምሶሶ ፡ ትተው
የሰውን ፡ ጉድፍ ፡ የሚያዩ ፡ አጥርተው
(፪x)

አዝ፦ መራመድ ፡ ሲያቅተኝ ፡ በጽድቅ ፡ ጐዳና
ነፍሴም ፡ ስትጨነቅ ፡ በኀጢአት ፡ ፈተና
ሥጋዬም ፡ ሲረክስ ፡ ጠፍቶ ፡ ህሊናዬ
እንደሰው ፡ መች ፡ ተወኝ (፪x) ፡ ጌታዬ
ጨክኖ ፡ መች ፡ ተወኝ (፪x) ፡ ጌታዬ

ይሄ ፡ ነው ፡ ብዬ ፡ የማልጨርሰው
ውለታ ፡ አለብኝ (፪x) ፡ ብዙ ፡ የማላውቀው
ይሄ ፡ ነው ፡ ብዬ ፡ የማልጨርሰው
ውለታ ፡ አለብኝ (፪x) ፡ ብዙ ፡ የማላውቀው