ያላየሁት ፡ ዓለም (Yalayehut Alem) - መስፍን ፡ ጉቱ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
መስፍን ፡ ጉቱ
(Mesfin Gutu)

Mesfin Gutu 7.jpg


(7)

ዛሬ ፡ ላይ ፡ ቆሜ ፡ ነገን ፡ አያለሁ
(Zarie Lay Qomie Negen Ayalehu)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፭ (2013)
ቁጥር (Track):

(6)

ርዝመት (Len.): 5:31
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የመስፍን ፡ ጉቱ ፡ አልበሞች
(Albums by Mesfin Gutu)

የተደረገልኝን ፡ አይቼ
ከአንተ ፡ የተቀበልኩትን ፡ አይቼ
በፊትህ ፡ ቅኔን ፡ ተቀኘሁኝ
እንዲህ ፡ አልኩኝ

አንተ ፡ ጌታዬ ፡ ነህ ፡ አንተ
ኧረ ፡ አንተ ፡ ንጉሤ ፡ ነህ ፡ አንተ
አንተ ፡ ጌታዬ ፡ ነህ ፡ አንተ
ኧረ ፡ አንተ ፡ አባቴ ፡ ነህ ፡ አንተ

ያላየሁት ፡ ዓለም ፡ ያልቀመስኩት ፡ ኑሮ
በጌታ ፡ ሆነልኝ ፡ ይገርማል ፡ ዘንድሮ
ተመስገን ፡ ነው ፡ እንጂ ፡ ሌላ ፡ ምን ፡ ይባላል
የአምላኬ ፡ ቅናት ፡ ይህንን ፡ አድርጓል
ተመስገን ፡ ነው ፡ እንጂ ፡ ሌላ ፡ ምን ፡ ይባላል
የአምላኬ ፡ ቅናት ፡ ይህንን ፡ አድርጓል (፪x)

እንዲህ ፡ ነው ፡ ጌታ ፡ ሲረዳ
እንዲህ ፡ ነው ፡ ኢየሱስ ፡ ሲያሳርፍ
(እንዲህ ፡ ነው ፡ ጌታ ፡ ሲረዳ
እንዲህ ፡ ነው ፡ ኢየሱስ ፡ ሲያሳርፍ) (፪x)

ደግሜ ፡ ደግሜ ፡ ጌታን ፡ አመልካለሁ
ጌታን ፡ አከብራለሁ (፪x)
እርሱ ፡ የእኔ ፡ አባት ፡ መድሃኒቴ ፡ ነው (፫x)
አቅም ፡ ብርቱ ፡ ሳለ ፡ ጉልበቴ ፡ ሳይደክም
ለዚህ ፡ ከንቱ ፡ ዓለም ፡ ልቤን ፡ አላዝልም
አቅም ፡ ብርቱ ፡ ሳለ ፡ ጉልበቴ ፡ ሳይደክም
ለዚህ ፡ ከንቱ ፡ ዓለም ፡ ልቤን ፡ አላዝልም (፪x)

እንደምን ፡ ይቻላል ፡ ያለ ፡ ጌታ ፡ ሆኖ
በራስ ፡ መተማመን ፡ ድጋፍ ፡ ተሸፍኖ
ዓለምን ፡ ናቅ ፡ አድርጐ ፡ ጌታን ፡ መወዳጀት
ይህ ፡ ታላቅ ፡ ጥበብ ፡ ነው ፡ የሠማይ ፡ በረከት
ዓለምን ፡ ናቅ ፡ አድርጐ ፡ ጌታን ፡ መወዳጀት
ይህ ፡ ታላቅ ፡ ጥበብ ፡ ነው ፡ የሠማይ ፡ በረከት (፪x)

እንዲህ ፡ ነው ፡ ጌታ ፡ ሲረዳ
እንዲህ ፡ ነው ፡ ኢየሱስ ፡ ሲያሳርፍ
(እንዲህ ፡ ነው ፡ ጌታ ፡ ሲረዳ
እንዲህ ፡ ነው ፡ ኢየሱስ ፡ ሲያሳርፍ) (፫x)