ትዝ ፡ ይለኛል (Tez Yelegnal) - መስፍን ፡ ጉቱ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
መስፍን ፡ ጉቱ
(Mesfin Gutu)

Mesfin Gutu 3.png


(3)

ተሻገር ፡ ያለው
(Teshager Yalew)

ዓ.ም. (Year): ፲ ፱ ፻ ፺ ፮ (2004)
ቁጥር (Track):

(7)


ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የመስፍን ፡ ጉቱ ፡ አልበሞች
(Albums by Mesfin Gutu)

 
አንተ ፡ የኔ ፡ የራሴ ፡ የግሌ ፡ የኔ
ባስጨናቂው ፡ ለት ፡ ለኔ ፡ ደርሰህ
በጨለማ ፡ እኔ ፡ ላይ ፡ ብርሃን ፡ ይብራ ፡ ብለህ
ታሪኬን ፡ ለውጠህ ፣ ታዲያ ፡ ልበልህ ፡ እንጂ ፡ አንተ ፡ የኔ (፪x)
 
ማን ፣ ኧረ ፡ ማን ፣ ማን ይወስድብኛል ፡ አንተን ፡ ከኔ (፪x)
ማን ፣ ኧረ ፡ ማን ፣ ማን ይወስድብኛል ፡ አንተን ፡ ከኔ (፪x)
ተማመለህ ፡ እኮ ፡ ነው ፡ የኔ ፡ ጌታ
በጭንቅ ፡ የወለድከኝ ፡ በጎልጎታ
እድሜዬን ፡ በሙሉ ፡ ሰጥሃለሁ
ዘላለም ፡ ለቃልህ ፡ እገዛለሁ ፣ እገዛለሁ
 
ታዲያ ፣ ልዘምር ፡ እንጂ
ልቀኝ ፡ እንጂ
ለባለውለታዬ ፡ ልኑር ፡ እንጂ ፡ አሃሃሃ
ታዲያ ፡ ታዲያ (፪x)
 
እንደመሸ ፡ አይቀርም ፡ ለሊቱ ፡ ይነጋል (፬x)
ማንጋት ፡ ልማድህ ፡ ነውና ፣ ማንሳት ፡ ልማድህ ፡ ነወና
ማክበር ፡ ልማድህ ፡ ነወና ፣ ማስዋብ ፡ ልማድህ ፡ ነውና


ውዴ ፡ የኔ ፡ ነው ፡ እኔም ፡ ደግሞ ፡ የእርሱ ፡ ነኝ ፡ የየሱስ ፡ ነኝ (፪x)
ማንም ፡ አይገባም ፡ በመሀላችን
ጉድለት ፡ የሌለበት ፡ ነው ፡ ፍቅራችን
ጊዜም ፡ ሁኔታም ፡ አይሽረዉም ፡ ለኔስ ፡ ኢየሱሴ ፡ ልዩ ፡ ነዉ ፣ ልዩ ፡ ነዉ
 
ታዲያ ፣ ልዘምር ፡ እንጂ
ልቀኝ ፡ እንጂ
ለባለውለታዬ ፡ ልኑር ፡ እንጂ ፡ አሃሃሃ
ታዲያ ፡ ታዲያ (፪x)


አንተ ፡ የኔ ፡ የራሴ ፡ የግሌ ፡ የኔ
ባስጨናቂው ፡ ለት ፡ ለኔ ፡ ደርሰህ
በጨለማ ፡ እኔ ፡ ላይ ፡ ብርሃን ፡ ይብራ ፡ ብለህ
ታሪኬን ፡ ለውጠህ ፣ ታዲያ ፡ ልበልህ ፡ እንጂ ፡ አንተ ፡ የኔ (፪x)