ኧረ ፡ ስንቱ ፡ ታለፈ (Ere Sentu Talefe) - መስፍን ፡ ጉቱ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
መስፍን ፡ ጉቱ
(Mesfin Gutu)

Mesfin Gutu 3.png


(3)

ተሻገር ፡ ያለው
(Teshager Yalew)

ዓ.ም. (Year): ፲ ፱ ፻ ፺ ፮ (2004)
ቁጥር (Track):

(3)


ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የመስፍን ፡ ጉቱ ፡ አልበሞች
(Albums by Mesfin Gutu)

 
ኧረ ፡ ስንቱ ፡ ስንቱ ፡ ስንቱ ፡ ስንቱ ፡ ታለፈ
ኢየሱስ ፡ እየቀደመ ፡ ወዳጄ ፡ እየቀደመ
ውድዬ ፡ እየቀደመ (፪x)

ስንቱን ፡ ተራራ ፡ ባንተ ፡ አለፍኩኝ
ስንቱን ፡ ሸለቆ ፡ ውሃ ፡ ሞላኸው
ጌታዬ ፡ ባንተ ፡ ሁሉ ፡ ሆነልኝ
ክብር ፡ ምስጋና ፡ ላንተ ፡ ይድረስህ (፪x)

በሕይወቴ ፡ በኑሮዬ ፡ ጣልቃ ፡ እየገባህ
ጣልቃ ፡ እየገባህ ፡ ጣልቃ ፡ እየገባህ ፡ መንገዴን ፡ አቀና
ጣልቃ ፡ እየገባህ ፡ መንገዴን ፡ አቀና (፪x)

በአምላኬ ፡ ክንዱ ፡ ላይ ፡ ተደግፌ
በርሱ ፡ ደግነት ፡ አምናን ፡ አልፌ
ዘንድሮን ፡ አየሁ ፡ ጌታን ፡ ታምኜ
ላከብረው ፡ መጣሁ ፡ ሁሉንም ፡ ትቼ (፪x)

በሕይወቴ ፡ በኑሮዬ ፡ ጣልቃ ፡ እየገባህ
ጣልቃ ፡ እየገባህ ፡ ጣልቃ ፡ እየገባህ ፡ መንገዴን ፡ አቀናህ
ጣልቃ ፡ እየገባህ ፡ መንገዴን ፡ አቀናህ (፪x)

ማዕረጌ ፡ ነህ ፡ ማዕረጌ ፡ ነህ
ሁሉን ፡ ያለፍኩብህ ፡ ሁሉን ፡ ያለፍኩብህ
ሁሉን ፡ ያለፍኩብህ ፡ ሁሉን ፡ ያለፍኩብህ (፪x)

አምላኬ ፡ አምላኬ ፡ አምላኬ ፡ አምላኬ
አምላኬ ፡ መታመኛዬ ፡ አንተ ፡ ነህ ፡ ለኔ ፡ ክብሬ
ጌትዬ ፡ መታመኛዬ ፡ አንተ ፡ ነህ ፡ ለኔ ፡ ክብሬ
ውድዬ ፡ መታመኛዬ ፡ አንተ ፡ ነህ ፡ ለኔ ፡ ክብሬ
ኢየሱስ ፡ መታመኛዬ ፡ አንተ ፡ ነህ ፡ ለኔ ፡ ክብሬ (፪x­)