አባት ፡ አለኝ (Abat Alegn) - መስፍን ፡ ጉቱ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
መስፍን ፡ ጉቱ
(Mesfin Gutu)

Mesfin Gutu 3.png


(3)

ተሻገር ፡ ያለው
(Teshager Yalew)

ዓ.ም. (Year): ፲ ፱ ፻ ፺ ፮ (2004)
ቁጥር (Track):

፲ ፪ (12)


ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የመስፍን ፡ ጉቱ ፡ አልበሞች
(Albums by Mesfin Gutu)

 
ማዕበሉን ፡ በስልጣን ፡ የሚገስጽልኝ
ዞር ፡ በል ፡ የሚልልኝ
አባት ፡ አለኝ ፡ እኔ ፡ አባት ፡ አለኝ (፪x)
ረዳት ፡ አለኝ ፡ እኔ ፡ ረዳት ፡ አለኝ (፪x)

ከእናት ፡ ካባቴም ፡ በላይ ፡ ለኔ ፡ ራርተህ ፡ ስላየሁ (አሃሃ ፡ አሃ)
እንደ ፡ እግዚአብሔር ፡ ያለ ፡ ማንም ፡ የለም ፡ እላለሁ
ስደክም ፡ አበርትተህ ፡ ራሴን ፡ በዘይት ፡ ቀባህ (አሃሃ ፡ አሃ)
ጽዋዬም ፡ ተረፈልኝ ፡ ኢየሱስ ፡ ክብርህ ፡ ይስፋ
ጌታ ፡ ክብርህ ፡ ይስፋ ፡ ውዴ ፡ ክብርህ ፡ ይስፋ (፪x)

ሰው ፡ ቢጥል ፡ እግዚአብሔር ፡ ያነሳል (ሰው ፡ ቢጥል)
ሰው ፡ ቢጥል ፡ እግዚአብሔር ፡ ያነሳል
ከብሮ ፡ ያከብራል ፡ ከፍ ፡ ያደርጋል
ሰው ፡ ቢጥል ፡ እግዚአብሔር ፡ ያነሳል (ሰው ፡ ቢጥል) (፪x)

እንቅልፍ ፡ እንደያዘው ፡ እንደተኛ ፡ ሰው (፪x)
መስሎኝ ፡ ነበር ፡ እኔስ ፡ ግድ ፡ ማይለው (፪x)
ኧረ ፡ ይሄስ ፡ ሰው ፡ ሃይለኛ ፡ ነው ፡ ተነሳና ፡ ዞር ፡ በል አለው
ኧረ ፡ ይሄስ ፡ ሰው ፡ ሃይለኛ ፡ ነው ፡ ተነሳና ፡ ጸጥ ፡ በል ፡ አለው

አዝ፦ማዕበሉን ፡ በስልጣን ፡ የሚገስጽልኝ
ዞር ፡ በል ፡ የሚልልኝ
አባት ፡ አለኝ ፡ እኔ ፡ አባት ፡ አለኝ (፪x)
ረዳት ፡ አለኝ ፡ እኔ ፡ ረዳት ፡ አለኝ (፪x)

የምስኪን ፡ ወዳጅ ፡ ሆነህ ፡ በጐጆዬ ፡ ውስጥ ፡ ገባህ (አሃሃ ፡ አሃ)
የዘመመው ፡ ቤቴ ፡ ይኸው ፡ ባንተ ፡ ቀና
ታዲያ ፡ ልዘምር ፡ እንጂ ፡ ለምን ፡ ላጉረምርም (አሃሃ ፡ አሃ)
በጐጆዬ ፡ ውስጥ ፡ ያለው ፡ ኢየሱስ ፡ ይክበር ፡ ውድዬ ይክበር
ጌትዬ ፡ ይክበር ፡ ወድዬ ፡ ይክበር

አዝ፦ማዕበሉን ፡ በስልጣን ፡ የሚገስጽልኝ
ዞር ፡ በል ፡ የሚልልኝ
አባት ፡ አለኝ ፡ እኔ ፡ አባት ፡ አለኝ (፪x)
ረዳት ፡ አለኝ ፡ እኔ ፡ ረዳት ፡ አለኝ (፪x)