ውለታው ፡ አለብኝ (Wuletaw Alebegn) - መስፍን ፡ ጉቱ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
መስፍን ፡ ጉቱ
(Mesfin Gutu)

Mesfin Gutu 4.jpg


(4)

ታለፈ ፡ ያ ፡ ዘመን
(Talefe Ya Zemen)

ዓ.ም. (Year): ፲ ፱ ፻ ፺ ፱ (2007)
ቁጥር (Track):

(3)


ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የመስፍን ፡ ጉቱ ፡ አልበሞች
(Albums by Mesfin Gutu)

በጠላቴ ፡ መንደር ፡ በድል ፡ ላራመደኝ ፡ ኦሆ ፡ ላራመደኝ (፪x)
እኔስ ፡ የዚህ ፡ ጌታ ፡ ውለታው ፡ አለብኝ ፡ ኦሆ ፡ አለብኝ (፪x)
በክብር ፡ ላይ ፡ ክብር ፡ ክብርን ፡ ላለበሰኝ ፡ ኦሆ ፡ ላስታጠቀኝ (፪x)
ምነው ፡ ከዚህ ፡ በላይ ፡ እኔስ ፡ በሆንኩለት ፡ ኦሆ ፡ በሆንኩለት (፬x)

ዘመኑ ፡ የድል ፡ ነው ፡ የመከናዎን
ከአምላኬ ፡ የሰማሁት ፡ በመንፈስ ፡ ያወኩት ፡ የተረዳሁት
ዘመኑ ፡ የድል ፡ ነው ፡ የመከናዎን
ዘመኑ ፡ የድል ፡ ነው ፡ የመከናዎን (፪x)

በጠራራ ፡ ጸሐይ ፡ ደመናም ፡ ሳይታይ ፡ ኦሆ ፡ ደመናም ፡ ሳይታይ (፪x)
ምንጭን ፡ አፈለቀ ፡ ጌታ ፡ ከዓለቱ ፡ ላይ ፡ ኦሆ ፡ ጌታ ፡ ከዓለቱ ፡ ላይ (፪x)
እኔ ፡ ምስክር ፡ ነኝ ፡ ከዓለቱ ፡ ጠጥቼ ፡ ኦሆ ፡ ከዓለቱ ፡ ጠጥቼ (፪x)
ዘመኑ ፡ የድል ፡ ነው ፡ እላለሁኝ ፡ ዛሬ ፡ ኦሆ ፡ እላለሁኝ ፡ ዛሬ (፬x)

ተረጋጋሁ ፡ መንፈሱ ፡ ሲነካኝ ፡ ተረጋጋሁ
ተረጋጋሁ ፡ ቅባቱ ፡ ሲነካኝ ፡ ተረጋጋሁ
አመለጥኩኝ ፡ ወዳጄን ፡ ሰምቼው ፡ አመለጥኩኝ
አመለጥኩኝ ፡ ጌታዬን ፡ ሰምቼው ፡ አመለጥኩኝ (፪x)