ገና ፡ ከጅምሩ (Gena Kejemeru) - መስፍን ፡ ጉቱ ፡ እና ፡ ቴዎድሮስ ፡ ታደሰ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
መስፍን ፡ ጉቱ ፡ እና ፡ ቴዎድሮስ ፡ ታደሰ
(Mesfin & Teddy)

Mesfin & Teddy Esp.jpg

ልዩ ፡ እትም
(Esp)

ሰላም ፡ ነው
(Selam New)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፫ (2010)
ቁጥር (Track):

(3)

ርዝመት (Len.): 5:35
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የመስፍን ፡ ጉቱ ፡ እና ፡ ቴዎድሮስ ፡ ታደሰ ፡ አልበሞች
(Albums by Mesfin & Teddy)

አዝ፦ ገና ፡ ከጅምሩ ፡ ውድቀቴን ፡ ሲጠባበቁ
በትንሽ ፡ በትልቁ ፡ ድካሜ ፡ ሲሳለቁ (፪x)

ልቤ ፡ በጌታ ፡ ላይ ፡ አበረታሁና
ዛሬ ፡ ከፍታ ፡ ላይ ፡ ወጣሁ ፡ ለምሥጋና (፪x)

ጅማሬዬ ፡ ታናሽ ፡ ቢመስል ፡ ፍፃሜዬ ፡ የአማረ ፡ ነው
ያለኝን ፡ ጌታ ፡ ሰምቼ ፡ በቤቱ ፡ ፀንቻለሁ
ሟርተኞች ፡ የሟረቱ ፡ ስንቶች ፡ ተነስተው ፡ ቢሞቱ
የጠራኝ ፡ የቀባኝ ፡ ጌታ ፡ አይጥለኝ ፡ ለአፍታ

ከሳሼ ፡ ያልገባው ፡ አንድ ፡ ነገር
አባቴ ፡ መሆኑን ፡ እግዚአብሔር
ሊከሰኝ ፡ ቢፈልግ ፡ ፍርድ ፡ የእኔ ፡ ነው
ይህን ፡ እንኳን ፡ የማያቅ ፡ ምኑ ፡ ሞኝ ፡ ነው (፪x)

አዝ፦ ገና ፡ ከጅምሩ ፡ ውድቀቴን ፡ ሲጠባበቁ
በትንሽ ፡ በትልቁ ፡ ድካሜ ፡ ሲሳለቁ (፪x)

ልቤ ፡ በጌታ ፡ ላይ ፡ አበረታሁና
ዛሬ ፡ ከፍታ ፡ ላይ ፡ ወጣሁ ፡ ለምሥጋና (፪x)

የማያልፍ ፡ የመሰለኝ ፡ ያ ፡ ዘመን ፡ ካለፈልኝ
ነገንም ፡ በእርሱ ፡ ላይ ፡ ጥዬ ፡ ልዘምር ፡ ተደላድዬ
አቤኔዘር ፡ ሆኖኛልና ፡ ልጨምር ፡ ብዙ ፡ ምሥጋና
ለረዳኝ ፡ ላገዘኝ ፡ ጌታ ፡ ለሆነኝ ፡ እድል ፡ ፈንታ

ከሳሼ ፡ ያልገባው ፡ አንድ ፡ ነገር
አባቴ ፡ መሆኑን ፡ እግዚአብሔር
ሊከሰኝ ፡ ቢፈልግ ፡ ፍርድ ፡ የእኔ ፡ ነው
ይህን ፡ እንኳን ፡ የማያቅ ፡ ምኑ ፡ ሞኝ ፡ ነው (፪x)

አዝ፦ ገና ፡ ከጅምሩ ፡ ውድቀቴን ፡ ሲጠባበቁ
በትንሽ ፡ በትልቁ ፡ ድካሜ ፡ ሲሳለቁ (፪x)

ልቤ ፡ በጌታ ፡ ላይ ፡ አበረታሁና
ዛሬ ፡ ከፍታ ፡ ላይ ፡ ወጣሁ ፡ ለምሥጋና (፪x)

ከሳሼ ፡ ያልገባው ፡ አንድ ፡ ነገር
አባቴ ፡ መሆኑን ፡ እግዚአብሔር
ሊከሰኝ ፡ ቢፈልግ ፡ ፍርድ ፡ የእኔ ፡ ነው
ይህን ፡ እንኳን ፡ የማያቅ ፡ ምኑ ፡ ሞኝ ፡ ነው (፬x)