እንዴት ፡ ልፍራ (Endiet Lefra) - መስፍን ፡ ጉቱ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
መስፍን ፡ ጉቱ
(Mesfin Gutu)

Mesfin Gutu Esp.png

ልዩ ፡ እትም
(Esp)

እንዲሁ ፡ በዋዛ
(Endihu Bewaza)

ዓ.ም. (Year): ፲ ፱ ፻ ፺ ፰ (2005)
ቁጥር (Track):

፲ ፩ (11)

ርዝመት (Len.): 4:26
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የመስፍን ፡ ጉቱ ፡ አልበሞች
(Albums by Mesfin Gutu)

እንዴት ፡ ልፍራ ፡ እንዴት ፡ ልሸበር
እግዚአብሔር ፡ ሆኖልኝ ፡ ሞገስ (፪x)

አምላካችን ፡ መጠጊያችንና ፡ ኃይላችን ፡ ነህ
ባገኘን ፡ በታላቅ ፡ መከራ ፡ ረዳታችን ፡ አሃሃ ፡ ረዳታችን
ስለዚህ ፡ ምድር ፡ ብትናወጥ
ተራሮች ፡ ወደባሕር ፡ ልብ ፡ ቢወሰዱ
እኔ ፡ አልፈራም ፡ አሃሃ ፡ እኔ ፡ አልፈራም

ማለፍ ፡ የማይቻለውን ፡ በአንተ ፡ አለፍኩ
አስፈሪውን ፡ ጨለማ ፡ ተሻገርኩኝ (፫x)
ሁሉን ፡ በአንተ ፡ አለፍኩኝ
ክብርህን ፡ ይኸው ፡ አየሁ ፡ ጨለማው ፡ ሰገፈፍ
አዲስ ፡ ቀን ፡ ወጣልኝ ፡ ክበር ፡ ያከበርከኝ

አምላካችን ፡ መጠጊያችንና ፡ ኃይላችን ፡ ነህ
ባገኘን ፡ በታላቅ ፡ መከራ ፡ ረዳታችን ፡ አሃሃ ፡ ረዳታችን
ስለዚህ ፡ ምድር ፡ ብትናወጥ
ተራሮች ፡ ወደባሕር ፡ ልብ ፡ ቢወሰዱ
እኔ ፡ አልፈራም ፡ አሃሃ ፡ እኔ ፡ አልፈራም

ለህዝቡ ፡ የሚያዝን ፡ ፍፁም ፡ የሚራራ
አማኑኤል ፡ አለ ፡ ዛሬም ፡ ከኛ ፡ ጋራ (፫x)
ስናዝን ፡ አፅናንቶን ፡ ኃይልም ፡ ጉልበት ፡ ሰጥቶን
መከራችንን ፡ ረሳን ፡ አምላካችን ፡ በእኛ ፡ ከብሮ