በአንተ ፡ የታሰበ (Bante Yetasebe) - መስፍን ፡ ጉቱ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
መስፍን ፡ ጉቱ
(Mesfin Gutu)

Mesfin Gutu Esp.png

ልዩ ፡ እትም
(Esp)

እንዲሁ ፡ በዋዛ
(Endihu Bewaza)

ዓ.ም. (Year): ፲ ፱ ፻ ፺ ፰ (2005)
ቁጥር (Track):

(9)

ርዝመት (Len.): 4:13
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የመስፍን ፡ ጉቱ ፡ አልበሞች
(Albums by Mesfin Gutu)

ሠማያቶች ፡ ይስሙ ፣ ይስሙ ፡ ምድር ፡ ታስተጋባ
የምቀኘውን ፡ ቅኔ ፡ ያለኝን ፡ ምሥጋና
የከንፈሬን ፡ ፍሬ ፣ ፍሬ ፡ በፊቱ ፡ ላፍስሰው
ትናንት ፡ እንዳዜምኩት ፡ ደስታዬ ፡ በአንተው ፡ ነው

በአንተ ፡ የታሰበ ፡ የተረዳ ፡ ሰው
ጌታ ፡ እንደ ፡ እኔ ፡ ማነው (፪x)

እንደ ፡ እኔ ፡ ማነው ፡ ክብር ፡ ያየው
እንደ ፡ እኔ ፡ ማነው ፡ ወግ ፡ ያየው
እንደ ፡ እኔ ፡ ማነው ፡ ደስ ፡ ያለው

እንደ ፡ እኔ ፡ ማነው ፡ ክብር ፡ ያየው
እንደ ፡ እኔስ ፡ ማነው ፡ ወግ ፡ ያየው (፪x)

በሄድኩበት ፡ ሁሉ ፣ ሁሉ ፡ ስለ ፡ አንተ ፡ አወራለሁ
ስላደረክልኝ ፡ ድንቅ ፡ ቆሜ ፡ ዘምራለሁ
ከአደረከው ፡ አንዳች ፣ አንዳች ፡ አልጐደለብኝም
ምርጫዬ ፡ ነህ ፡ አንተስ ፡ እስከ ፡ ለዘለዓለም

በአንተ ፡ የታሰበ ፡ የተረዳ ፡ ሰው
ጌታ ፡ እንደ ፡ እኔ ፡ ማነው (፪x)

እንደ ፡ እኔ ፡ ማነው ፡ ክብር ፡ ያየው
እንደ ፡ እኔስ ፡ ማነው ፡ ወግ ፡ ያየው (፮x)