አበቃ (Abeqa) - መስፍን ፡ ጉቱ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
መስፍን ፡ ጉቱ
(Mesfin Gutu)

Mesfin Gutu Esp.png

ልዩ ፡ እትም
(Esp)

እንዲሁ ፡ በዋዛ
(Endihu Bewaza)

ዓ.ም. (Year): ፲ ፱ ፻ ፺ ፰ (2005)
ቁጥር (Track):

(6)

ርዝመት (Len.): 5:03
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የመስፍን ፡ ጉቱ ፡ አልበሞች
(Albums by Mesfin Gutu)

አበቃ ፡ አከተመ ፡ በተባለ ፡ ጊዜ
ማነው ፡ ለእኔስ ፡ ፈጥኖ ፡ የደረሰው (፪x)

ጌታ ፡ እኮ ፡ ነው
ጌታ ፡ እኮ ፡ ነው ፡ አሃ
(፫x)
ጌታ ፡ እኮ ፡ ነው
ይህን ፡ ያደረገው

እስራቴን ፡ ፈተህ ፡ ቀንበሬን ፡ ሰብረህ
ያስጨነቀኝ ፡ ጠላት ፡ ከእግሬ ፡ ሥር ፡ ጥለህ
ዛሬማ ፡ ቀና ፡ አልኩኝ ፡ ይኸው ፡ በኢየሱስ
ዘለዓለም ፡ ልገዛ ፡ ልስገድልህ (፪x)

አምላክ ፡ እንደሌለው ፡ ለምን ፡ አዝናለሁ
ረዳት ፡ እንደሌለው ፡ ለምን ፡ አዝናለሁ
አባት ፡ እንደሌለው ፡ ለምን ፡ አዝናለሁ
ረዳት ፡ እንደሌለው ፡ ለምን ፡ አዝናለሁ

ሲረዳኝ ፡ በዓይኔ ፡ እያየሁ
ሲያግዘኝ ፡ በዓይኔ ፡ እያየሁ (፪x)

ሥምህን ፡ ጠርቼ ፡ ሁሉን ፡ አለፍኩ
መቼ ፡ አንተን ፡ ይዤ ፡ እኔስ ፡ አፈርኩ
ዛሬም ፡ የሚያቅተኝ ፡ ሁሉ
እወጣዋለሁ ፡ የአንተ ፡ ነው ፡ ኃይሉ (፪x)

አበቃ ፡ አከተመ ፡ በተባለ ፡ ጊዜ
ማነው ፡ ለእኔስ ፡ ፈጥኖ ፡ የደረሰው (፪x)

ጌታ ፡ እኮ ፡ ነው
ጌታ ፡ እኮ ፡ ነው ፡ አሃ
(፫x)
ጌታ ፡ እኮ ፡ ነው
ይህን ፡ ያደረገው

አምላክ ፡ እንደሌለው ፡ ለምን ፡ አዝናለሁ
ረዳት ፡ እንደሌለው ፡ ለምን ፡ አዝናለሁ
አባት ፡ እንደሌለው ፡ ለምን ፡ አዝናለሁ
ረዳት ፡ እንደሌለው ፡ ለምን ፡ አዝናለሁ

ሲረዳኝ ፡ በዓይኔ ፡ እያየሁ
ሲያግዘኝ ፡ በዓይኔ ፡ እያየሁ (፪x)