Tesfaye Gabisso/Yenazretu Eyesus/Yemiquaquameh Manem Yelem

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ

ዘማሪ ተስፋዬ ጋቢሶ ርዕስ የሚቋቋምህ ማንም የለም አልበም የናዝሬቱ ኢየሱስ

አዝ የሚቋቋምህ ማንም የለም ፈቃድህ በእኛ ይሙላ ይፈፀም ታላቅነትህም ይነገር ጌታዬ ሆይ አንተ ብቻ ክበር (፪x)

ሕዝብህን ከምድር ዋጅተሃል ታላቅ ሥራ ጀምረሃል ሀሳብህ አይከለከልም ፅድቅህ እውነትህ ይለምልም

አዝ የሚቋቋምህ ማንም የለም ፈቃድህ በእኛ ይሙላ ይፈፀም ታላቅነትህም ይነገር ጌታዬ ሆይ አንተ ብቻ ክበር

በየደረስንበት ስፍራ ስራችንን አንተ ሥራ እጃችን ሳይዝል ስይደክም ዛሬም እንደ ወትሮ ቅደም

አዝ የሚቋቋምህ ማንም የለም ፈቃድህ በእኛ ይሙላ ይፈፀም ታላቅነትህም ይነገር ጌታዬ ሆይ አንተ ብቻ ክበር

ስለተነቀፈው ሥምህ በምርኮ ስላለው ሕዝብህ ይዘርጋ ያ ፅኑ ክንድህ ዛሬም ይንሰራፋ ክብርህ

አዝ የሚቋቋምህ ማንም የለም ፈቃድህ በእኛ ይሙላ ይፈፀም ታላቅነትህም ይነገር ጌታዬ ሆይ አንተ ብቻ ክበር

ወድቀን በፊትህ ስንጮህ ክንድህ ከፍ ይበል ጌታ ሆይ ሰማይ ምድሩ ያከብርሃል ሁሉም በፊትህ ይሰግዳል

አዝ የሚቋቋምህ ማንም የለም ፈቃድህ በእኛ ይሙላ ይፈፀም ታላቅነትህም ይነገር ጌታዬ ሆይ አንተ ብቻ ክበር (፪x)