የሚቋቋምህ ፡ ማንም ፡ የለም (Yemiquaquameh Manem Yelem) - ተስፋዬ ፡ ጋቢሶ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ተስፋዬ ፡ ጋቢሶ
(Tesfaye Gabisso)

Lyrics.jpg


(5)

የናዝሬቱ ፡ ኢየሱስ
(Yenazretu Eyesus)

ቁጥር (Track):

፲ ፬ (14)

ርዝመት (Len.): 3:16
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የተስፋዬ ፡ ጋቢሶ ፡ አልበሞች
(Albums by Tesfaye Gabisso)

አዝ፦ የሚቋቋምህ ፡ ማንም ፡ የለም
ፈቃድህ ፡ በእኛ ፡ ይሙላ ፡ ይፈፀም
ታላቅነትህም ፡ ይነገር
ጌታዬ ፡ ሆይ ፡ አንተ ፡ ብቻ ፡ ክበር (፪x)

ሕዝብህን ፡ ከምድር ፡ ዋጅተሃል
ታላቅ ፡ ሥራ ፡ ጀምረሃል
ሀሳብህ ፡ አይከለከልም
ፅድቅህ ፡ እውነትህ ፡ ይለምልም

አዝ፦ የሚቋቋምህ ፡ ማንም ፡ የለም
ፈቃድህ ፡ በእኛ ፡ ይሙላ ፡ ይፈፀም
ታላቅነትህም ፡ ይነገር
ጌታዬ ፡ ሆይ ፡ አንተ ፡ ብቻ ፡ ክበር

በየደረስንበት ፡ ስፍራ
ስራችንን ፡ አንተ ፡ ሥራ
እጃችን ፡ ሳይዝል ፡ ስይደክም
ዛሬም ፡ እንደ ፡ ወትሮ ፡ ቅደም

አዝ፦ የሚቋቋምህ ፡ ማንም ፡ የለም
ፈቃድህ ፡ በእኛ ፡ ይሙላ ፡ ይፈፀም
ታላቅነትህም ፡ ይነገር
ጌታዬ ፡ ሆይ ፡ አንተ ፡ ብቻ ፡ ክበር

ስለተነቀፈው ፡ ሥምህ
በምርኮ ፡ ስላለው ፡ ሕዝብህ
ይዘርጋ ፡ ያ ፡ ፅኑ ፡ ክንድህ
ዛሬም ፡ ይንሰራፋ ፡ ክብርህ

አዝ፦ የሚቋቋምህ ፡ ማንም ፡ የለም
ፈቃድህ ፡ በእኛ ፡ ይሙላ ፡ ይፈፀም
ታላቅነትህም ፡ ይነገር
ጌታዬ ፡ ሆይ ፡ አንተ ፡ ብቻ ፡ ክበር

ወድቀን ፡ በፊትህ ፡ ስንጮህ
ክንድህ ፡ ከፍ ፡ ይበል ፡ ጌታ ፡ ሆይ
ሰማይ ፡ ምድሩ ፡ ያከብርሃል
ሁሉም ፡ በፊትህ ፡ ይሰግዳል

አዝ፦ የሚቋቋምህ ፡ ማንም ፡ የለም
ፈቃድህ ፡ በእኛ ፡ ይሙላ ፡ ይፈፀም
ታላቅነትህም ፡ ይነገር
ጌታዬ ፡ ሆይ ፡ አንተ ፡ ብቻ ፡ ክበር (፪x)