የአደባባይ ፡ ሰው ፡ ሆነህ (Yeadebabay Sew Honeh) - ተስፋዬ ፡ ጋቢሶ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ተስፋዬ ፡ ጋቢሶ
(Tesfaye Gabisso)

Lyrics.jpg


(5)

የናዝሬቱ ፡ ኢየሱስ
(Yenazretu Eyesus)

ቁጥር (Track):

(3)

ርዝመት (Len.): 3:41
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የተስፋዬ ፡ ጋቢሶ ፡ አልበሞች
(Albums by Tesfaye Gabisso)

የአደባባይ ፡ ሰው ፡ ሆነህ
በየማዕዘኑ ፡ ላይ ፡ ቆመህ
ሰውን ፡ አይተህ ፡ በሰው ፡ ታይተህ (፪x)
በስወር ፡ አይቶ ፡ በግልጥ ፡ የሚከፍልህን
በከፍታ ፡ ላይ ፡ የሚያስኬድህን
ረስተህ ፡ የለም ፡ ወይ ፡ አሳዳጊ ፡ ጌታህን

በስውር ፡ የሚቀመጡ
ጌታቸውን ፡ የሚያደምጡ
የሕይወትን ፡ ቃል ፡ የሚያመጡ (፪x)
ሰውን ፡ ለማነጽ ፡ ነቅተው ፡ የሚታጠቁ
ለበጐ ፡ ሥራ ፡ ሁሉ ፡ የሚበቁ
ምስጉኖች ፡ ናቸው ፡ መማለድን ፡ የሚያዉቁ

ከእግዚአብሔር ፡ የተላከ
እርሱ ፡ ነው ፡ የተባረከ
ቃሉን ፡ ብቻ ፡ እየሰበከ (፪x)
አንተንስ ፡ ማነው ፡ አስነስቶ ፡ የላከህ
በፍጻሜው ፡ ላይ ፡ ትጠየቃለህ
እንደ ፡ ሥራህም ፡ ያኔ ፡ ትከፈላለህ

ሥራህ ፡ ድካምህ ፡ ብዙ ፡ ነው
አንተነትህን ፡ ያጐላው
ጌታ ፡ እንዳይታይ ፡ የጋረደው (፪x)
እስኪ ፡ በእውነት ፡ መርምረው ፡ ሕይወትህን
መፀለይ ፡ ትተህ ፡ መራቆትህን
ኢየሱስን ፡ ጋርደህ ፡ አንተ ፡ መታየትህን

ስማው ፡ ኢየሱስ ፡ ይመክርሃል
"ተው ፣ እረፍ ፣ ፀልይ" ፡ ይልሃል
ከእግሮቹ ፡ ሥር ፡ ሥጋህን ፡ ጣል (፪x)
ያን ፡ ጊዜ ፡ ጌታ ፡ በሰገነት ፡ ላይ ፡ ወጥቶ
ለዓለም ፡ ይታያል ፡ ብርሃኑ ፡ በርቶ
ሕይወት ፡ ይበዛል ፡ የስንዴው ፡ ቅንጣት ፡ ሞቶ