From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ምሕረትና ፡ ዕውነት ፣ ፍቅር ፡ ቸርነት ፡ ከሞላው ፡ ጌታ
ኃጥዕ ፡ በንስሐ ፡ ይቀበል ፡ ይቅርታ
ማንም ፡ እንዳይጠፋ ፡ መድህን ፡ ሞቶልናል
ክርስቶስ ፡ ኢየሱስ ፡ ቤዛ ፡ ሆኖልናል
አዝ፦ የኃጢአተኛውን ፡ ጥፋት
እግዚአብሔር ፡ መቼ ፡ ይወዳል?
የተጣለ ፡ ሰው ፡ እንኳን ፡ ፈጽሞ ፡ እንዳይጠፋ
በምክሩ ፡ ያስባል ፣ በምክሩ ፡ ያስባል
ሰው ፡ ግን ፡ በውድቀቱ
ለምን ፡ ተስፋውን ፡ ይቆርጣል ፡ ቶሎ?
ለምን ፡ ይቀናዋል ፡ መውረድ ፡ አሽቆልቁሎ?
"ጌታን ፡ እጠብቃለሁ ፣ ቢገድለኝም" ፡ ብሎ
በዕምነት ፡ የሚቆም ፡ አይቀርም ፡ ጐስቁሎ
አዝ፦ የኃጢአተኛውን ፡ ጥፋት
እግዚአብሔር ፡ መቼ ፡ ይወዳል?
የተጣለ ፡ ሰው ፡ እንኳን ፡ ፈጽሞ ፡ እንዳይጠፋ
በምክሩ ፡ ያስባል ፣ በምክሩ ፡ ያስባል
የሚወደውን ፡ ልጅ ፡ እግዚአብሔር ፡ ለጥቅሙ ፡ ይቀጣዋል
መክሮ ፡ ይገስጸዋል ፣ ያስተካክለዋል
በአባትነት ፡ ዓይኑ ፡ ይመለከተዋል
ሲፍገመገም ፡ ቢያየው ፣ ፍጥኖ ፡ ይደግፈዋል
አዝ፦ የኃጢአተኛውን ፡ ጥፋት
እግዚአብሔር ፡ መቼ ፡ ይወዳል?
የተጣለ ፡ ሰው ፡ እንኳን ፡ ፈጽሞ ፡ እንዳይጠፋ
በምክሩ ፡ ያስባል ፣ በምክሩ ፡ ያስባል
|