ከዚህም ፡ የሚበልጥ (Kezihem Yemibelt) - ተስፋዬ ፡ ጋቢሶ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ተስፋዬ ፡ ጋቢሶ
(Tesfaye Gabisso)

Lyrics.jpg


(7)

አልበም
(kezihem yemibelt)

ቁጥር (Track):

፲ ፪ (12)

ርዝመት (Len.): 3:47
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የተስፋዬ ፡ ጋቢሶ ፡ አልበሞች
(Albums by Tesfaye Gabisso)

አዝ፦ ከዚህም ፡ የሚበልጥ
የጌታ ፡ ኃይል ፡ ሲገለጥ
እናያለን ፡ ገና ፣ የክብሩን ፡ ደመና
ምድር ፡ ስትሞላ ፣ በጌታ ፡ ምሥጋና

ጌታ ፡ በመንፈሱ ፡ በቅሉ ፡ መርምሮ
ሥራችንን ፡ ሁሉ ፡ ቢነግረን ፡ ዘርዝሮ
በዕውቀቱ ፡ ተደንቀን ፣ በኑሮአችን ፡ አፍረን
ንስሐ ፡ ገብተናል ፡ "ይቅር ፡ በለን" ፡ ብለን

አዝ፦ ከዚህም ፡ የሚበልጥ
የጌታ ፡ ኃይል ፡ ሲገለጥ
እናያለን ፡ ገና ፣ የክብሩን ፡ ደመና
ምድር ፡ ስትሞላ ፣ በጌታ ፡ ምሥጋና

ኃጢአታችንን ፡ በደሙ ፡ አነጻው
የእኛ ፡ ጌታ ፡ ኢየሱስ ፡ ይቅርታው ፡ ብዙ ፡ ነው
ርኩስ ፡ መናፍስትን ፡ በኃይሉ ፡ ያስወጣል
በወንጌሉ ፡ ሥልጣን ፡ መንግሥቱን ፡ ያሰፋል

አዝ፦ ከዚህም ፡ የሚበልጥ
የጌታ ፡ ኃይል ፡ ሲገለጥ
እናያለን ፡ ገና ፣ የክብሩን ፡ ደመና
ምድር ፡ ስትሞላ ፣ በጌታ ፡ ምሥጋና

"ጌታ ፡ ሆይ!" ፡ እያለ ፡ ለሚቃትተው
ማዳኑ ፡ ሊመጣ ፡ ጽድቁ ፡ ሊገለጥ ፡ ነው
የእግዚአብሔር ፡ ምሕረት ፡ ሁሉንም ፡ አብስሩ
የበረከት ፡ ዝናብ ፡ ይኸው ፡ ውሽንፍሩ

አዝ፦ ከዚህም ፡ የሚበልጥ
የጌታ ፡ ኃይል ፡ ሲገለጥ
እናያለን ፡ ገና ፣ የክብሩን ፡ ደመና
ምድር ፡ ስትሞላ ፣ በጌታ ፡ ምሥጋና

ረሃብተኛ ፡ ሲመገብ ፣ ልኡል ፡ ቃሉን ፡ ሲሰጥ
በጻድቅን ፡ ዕልልታ ፡ ምድር ፡ ስትናወጥ
በምሥጋና ፡ ዜማ ፡ በደስታ ፡ ዝማሬ
በታላቁ ፡ መከር ፡ የአገልግሎት ፡ ፍሬ

ከዚህም ፡ የሚበልጥ
የጌታ ፡ ኃይል ፡ ሲገለጥ
እናያለን ፡ ገና ፣ የክብሩን ፡ ደመና
ምድር ፡ ስትሞላ ፣ በጌታ ፡ ምሥጋና