ባለፍኩበት ፡ መንገድ (Balefkubet Menged) - ተስፋዬ ፡ ጋቢሶ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ተስፋዬ ፡ ጋቢሶ
(Tesfaye Gabisso)

Lyrics.jpg


(7)

አልበም
(Yayehal)

ቁጥር (Track):

(6)

ርዝመት (Len.): 5:11
ጸሐፊ (Writer): 16
(654156
Property "Writer" has been marked for restricted use.
)
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የተስፋዬ ፡ ጋቢሶ ፡ አልበሞች
(Albums by Tesfaye Gabisso)

--67.162.239.217 14:14, 11 ኦክቶበር 2020 (UTC):አዝ፦ ባለፍኩበት ፡ መንገድ ፡ ለእኔ ፡ ተጠንቅቆ
እዚህ ፡ ያደረሰኝ ፡ ከክፉ ፡ ጠብቆ
እስከ ፡ ፍጻሜውም ፡ ያቆመኛል ፡ ጌታ
ሃገሬ ፡ እገባለሁ ፡ እምነቴ ፡ ሳይፈታ (፪x)

ማዕበሉ ፡ ሳይጥለኝ ፣ ውኃ ፡ ሳያሰጥመኝ
እጄን ፡ በእጁ ፡ ይዞ ፡ ወንዝ ፡ አሻገረኝ
የፈተናው ፡ እሣት ፡ ወላፈን ፡ ሳይጐዳኝ
በጌታዬ ፡ ፀጋ ፡ በሕይወት ፡ አለፍኩኝ

አዝ፦ ባለፍኩበት ፡ መንገድ ፡ ለእኔ ፡ ተጠንቅቆ
እዚህ ፡ ያደረሰኝ ፡ ከክፉ ፡ ጠብቆ
እስከ ፡ ፍጻሜውም ፡ ያቆመኛል ፡ ጌታ
ሃገሬ ፡ እገባለሁ ፡ እምነቴ ፡ ሳይፈታ (፪x)

ከሕያዋን ፡ ጋራ ፡ ኖሬ ፡ እንዳከብረው
ፈተናን ፡ አልፌ ፡ እንዳመሰግነው
ኢየሱስ ፡ ከጐኔ ፡ ቆሞ ፡ አበረታኝ
ከአንበሣው ፡ አፍም ፡ ደጋግሞ ፡ አወጣኝ

አዝ፦ ባለፍኩበት ፡ መንገድ ፡ ለእኔ ፡ ተጠንቅቆ
እዚህ ፡ ያደረሰኝ ፡ ከክፉ ፡ ጠብቆ
እስከ ፡ ፍጻሜውም ፡ ያቆመኛል ፡ ጌታ
ሃገሬ ፡ እገባለሁ ፡ እምነቴ ፡ ሳይፈታ (፪x)

ሕይወቴን ፡ ለአምላኬ ፡ አደራ ፡ እየሰጠሁ
በእረኝነቱ ፡ ሥር ፡ ሳልሰጋ ፡ እኖራለሁ
ከክንፎቹ ፡ በታች ፡ እተማመናለሁ
በእርሱ ፡ ተጠብቄ ፡ አገሬ ፡ እገባለሁ

አዝ፦ ባለፍኩበት ፡ መንገድ ፡ ለእኔ ፡ ተጠንቅቆ
እዚህ ፡ ያደረሰኝ ፡ ከክፉ ፡ ጠብቆ
እስከ ፡ ፍጻሜውም ፡ ያቆመኛል ፡ ጌታ
ሃገሬ ፡ እገባለሁ ፡ እምነቴ ፡ ሳይፈታ (፪x)

ጌታ ፡ የሠራውን ፡ ድንቅ ፡ አስታውሳለሁ
ስላለፈው ፡ ዘመን ፡ አመሰግናለሁ
ከፊቴ ፡ ላለውም ፡ በእርሱ ፡ እደገፋለሁ
በዘለዓለም ፡ ክንዱ ፡ በእቅፉ ፡ እኖራለሁ

አዝ፦ ባለፍኩበት ፡ መንገድ ፡ ለእኔ ፡ ተጠንቅቆ
እዚህ ፡ ያደረሰኝ ፡ ከክፉ ፡ ጠብቆ
እስከ ፡ ፍጻሜውም ፡ ያቆመኛል ፡ ጌታ
ሃገሬ ፡ እገባለሁ ፡ እምነቴ ፡ ሳይፈታ (፪x)