አቤቱ ፡ ጌታችን (Abietu Gietachen) - ተስፋዬ ፡ ጋቢሶ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ተስፋዬ ፡ ጋቢሶ
(Tesfaye Gabisso)

Lyrics.jpg


(7)

አልበም
(Yayehal)

ዓ.ም. (Year): ፲ ፱ ፻ ፺ ፫ ((2012))
ቁጥር (Track):

(5)

ርዝመት (Len.): 4:36
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የተስፋዬ ፡ ጋቢሶ ፡ አልበሞች
(Albums by Tesfaye Gabisso)

አቤቱ ፡ ጌታችን፣ እስኪ ፡ እናመስግንህ
ለውለታህ ፡ ምላሽ ፡ "ክበር" ፡ እንበልህ

ሰይጣን ፡ እንደ ፡ ስንዴ ፡ ሊያበጥረን ፡ ሽቶ
ዕምነት ፡ ተስፋችንን ፡ ሊያጨልም ፡ ዝቶ
አምርሮ ፡ ቢነሣም ፡ እጅግ ፡ ተቆጥቶ
ተገዝቶ ፡ አየነው ፡ በአንተ ፡ ድል ፡ ተነሥቶ

ስለ ፡ ዕምነታችን ፣ ስለ ፡ ሕይወታችን
የተሟገትክልን ፣ ተመስገን ፡ ጌታችን

የተጓዝንበትን ፡ መንገድ ፡ ሊያቋርጥ
ጠላታችን ፡ አልፎ፡ እንቅፋት ፡ ቢያስቀምጥ
የተመሸገውን ፡ ከፍ ፡ ያለውን ፡ ቅጥሩን
አፈራርሰህ ፡ ጣልከው ፡ ኢየሱስ ፡ ተመስገን

አንተ ፡ ቅን ፡ የሆነን፡ መንገድ ፡ ታቀናለህ
የተዘጋውንም ፡ በር ፡ ትከፍትልናለህ

የሕዝብህን ፡ ስድብ ፡ ከምድር ፡ አስወግደህ
ከፊታቸውም ፡ ላይ ፡ እንባቸውን ፡ አብሰህ
ራሣቸውን ፡ በዘይት ፡ በሞገስ ፡ ቀብተህ
በምሥጋናቸውም ፡ አንተ ፡ ትነግሣለህ

ለታናሹ ፡ መንጋ ፡ በዝቷል ፡ ቸርነትህ
ክበር ፡ አምላካችን ፡ ዘላለም ፡ ልዑል ፡ ነህ

ግብዣን ፡ አዘጋጅተህ ፡ በክብር ፡ ጠራኸን
በንጉሥ ፡ ገበታ ፡ ይኸው ፡ አስቀመጥከን
በክርስቶስ ፡ ኢየሱስ ፡ በከበረው ፡ ሥፍራ
ነፍሣችን ፡ ጠገበች ፡ ከሕይወት ፡ እንጀራ

ፈቅደን ፡ ከልባችን ፡ እናመልክሃለን
ለዘለዓለሙም ፡ ለአንተ ፡ እንገዛለን