የዘለዓለም ፡ አምላክ (Yezelalem Amlak) - ተስፋዬ ፡ ጋቢሶ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ተስፋዬ ፡ ጋቢሶ
(Tesfaye Gabisso)

Tesfaye Gabisso Esp.jpg

ልዩ ፡ እትም
(Esp)

አልበም
(22345)

ቁጥር (Track):

(5)

ርዝመት (Len.): 3:02
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የተስፋዬ ፡ ጋቢሶ ፡ አልበሞች
(Albums by Tesfaye Gabisso)

አዝ የዘለዓለም ፡ አምላክ ፡ የዘመናት ፡ ንጉሥ
ሁሉ ፡ በሁሉ ፡ ነው ፡ የናዝሬቱ ፡ ኢየሱስ (፪x)

ማለዳ ፡ ማለዳ ፡ አዲስ ፡ ነው ፡ ኢየሱስ
አይሰለችም ፡ ከቶ ፡ አንተ ፡ እንኳን ፡ ብታምጽ
የመስቀሉ ፡ ቃል ፡ ፈውስ ፡ ነው ፡ ለሕይወት
አምነው ፡ ለተጠጉት ፡ ይሆናል ፡ መሰረት

አዝ የዘለዓለም ፡ አምላክ ፡ የዘመናት ፡ ንጉሥ
ሁሉ ፡ በሁሉ ፡ ነው ፡ የናዝሬቱ ፡ ኢየሱስ (፪x)

ለሰልፍ ፡ አዘጋጅቶ ፡ ኃይልን ፡ ያስታጥቃል
በላይ ፡ የቆሙትን ፡ ከበታች ፡ ይጥላል
በትንሳኤው ፡ ስልጣን ፡ ውጊያውን ፡ አካሂዶ
ምርኮን ፡ ሰብስብ ፡ አለው ፡ ጠላቱን ፡ አሳዶ

አዝ የዘለዓለም ፡ አምላክ ፡ የዘመናት ፡ ንጉሥ
ሁሉ ፡ በሁሉ ፡ ነው ፡ የናዝሬቱ ፡ ኢየሱስ (፪x)

ፍላጻን ፡ ወርውሮ ፡ ምሽግን ፡ ነደለ
በአምላኩ ፡ ተማምኖ ፡ ውጊያውን ፡ ቀጠለ
በደም ፡ ጐዳና ፡ ላይ ፡ የኢየሱስ ፡ ነው ፡ ድሉ
ብሎ ፡ ዘምሮለት ፡ ቆመ ፡ በዕጣ ፡ ክፍሉ

አዝ የዘለዓለም ፡ አምላክ ፡ የዘመናት ፡ ንጉሥ
ሁሉ ፡ በሁሉ ፡ ነው ፡ የናዝሬቱ ፡ ኢየሱስ (፪x)