ምህረቱ ፡ አያልቅምና (Meheretu Ayalqemena) - ተስፋዬ ፡ ጋቢሶ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ተስፋዬ ፡ ጋቢሶ
(Tesfaye Gabisso)

Tesfaye Gabisso Esp.jpg

ልዩ ፡ እትም
(Esp)

ምህረቱ ፡ አያልቅምና
(Meheretu Ayalqemena)

ቁጥር (Track):

(9)

ርዝመት (Len.): 3:43
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የተስፋዬ ፡ ጋቢሶ ፡ አልበሞች
(Albums by Tesfaye Gabisso)

በባቢሎን ፡ ወንዞች ፡ ማዶ ፡ አዝነን ፡ ተቀምጠን
ጽዮንን ፡ ባሰብናት ፡ ጊዜ ፡ እጅግ ፡ አለቀስን
የመጽናናት ፡ አምላክ ፡ ከላይ ፡ ግን ፡ ያየናል
እንባችንን ፡ ጠርጐ ፡ ስብራታችንን ፡ ይጠግንልናል

አዝ፦ ምህረቱ ፡ አያልቅምና
ለዘለዓለም ፡ ቸር ፡ ነውና
የማዳን ፡ ኃይሉን ፡ ላሳየን
በክንዱ ፡ ለሚጐበኘን
መልካሙን ፡ መዓዛ ፡ በምሥጋና ፡ አቅርቡለት
በዕልልታ ፡ ስገዱለት

የችግረኞችን ፡ ጩኸት ፡ ሰምቶ ፡ አይጨክንም
ምርጦቹን ፡ ከልቡ ፡ በፍፁም ፡ አያስጨንቅም
ጠላታቸው ፡ ሊበትን ፡ በነጐድጓድ ፡ አንቀጥቅጦ
ረድኤታቸው ፡ ከተፍ ፡ ይላል ፡ ከሰማያት ፡ በግርማው ፡ ተገልጦ

አዝ፦ ምህረቱ ፡ አያልቅምና
ለዘለዓለም ፡ ቸር ፡ ነውና
የማዳን ፡ ኃይሉን ፡ ላሳየን
በክንዱ ፡ ለሚጐበኘን
መልካሙን ፡ መዓዛ ፡ በምሥጋና ፡ አቅርቡለት
በዕልልታ ፡ ስገዱለት

በሥጋዎቻቸው ፡ የገነኑ ፡ ፈፅመው ፡ ሲወድቁ
እግዚአብሔርን ፡ በመታመን ፡ የሚጠባበቁ
በእንባቸው ፡ ፍሬ ፡ እያሸበረቁ
በክንፍ ፡ ይወጣሉ ፡ ይሮጣሉ ፡ ይከብራሉ ፡ እንደ ፡ ዕንቁ

አዝ፦ ምህረቱ ፡ አያልቅምና
ለዘለዓለም ፡ ቸር ፡ ነውና
የማዳን ፡ ኃይሉን ፡ ላሳየን
በክንዱ ፡ ለሚጐበኘን
መልካሙን ፡ መዓዛ ፡ በምሥጋና ፡ አቅርቡለት
በዕልልታ ፡ ስገዱለት

ለእኛ ፡ መጠጊያችን ፡ ጌታ ፡ እግዚአብሔራችን
በምንም ፡ አንፈራም ፡ እርሱ ፡ ኃይላችን ፡ ነው
ከሰይጣን ፡ አሽክላ ፡ ሥሙ ፡ ይጠብቀናል
ለአሞራም ፡ ሳይሰጠን ፡ በክንፎቹ ፡ አዝሎ ፡ ቤቱ ፡ ያገባናል

አዝ፦ ምህረቱ ፡ አያልቅምና
ለዘለዓለም ፡ ቸር ፡ ነውና
የማዳን ፡ ኃይሉን ፡ ላሳየን
በክንዱ ፡ ለሚጐበኘን
መልካሙን ፡ መዓዛ ፡ በምሥጋና ፡ አቅርቡለት
በዕልልታ ፡ ስገዱለት (፪x)