ለእኔም፡ ያንን ፡ ፀጋ (Lenem Yanen Tsega) - ተስፋዬ ፡ ጋቢሶ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ተስፋዬ ፡ ጋቢሶ
(Tesfaye Gabisso)

Tesfaye Gabisso Esp.jpg

ልዩ ፡ እትም
(Esp)

አልበም
(Merehetu Ayalqemena)

ቁጥር (Track):

፲ ፭ (15)

ርዝመት (Len.): 4:29
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የተስፋዬ ፡ ጋቢሶ ፡ አልበሞች
(Albums by Tesfaye Gabisso)

የመከራ ፡ እቶን ፡ የማንጠሪያ ፡ እሳት
የመፈተኛ ፡ ፍም ፡ የመመዘኛ ፡ ጣት
ነበር ፡ በጀግኖች ፡ ዘንድ ፡ ባለፉት ፡ ጦረኞች
ባለፉበት ፡ መንገድ ፡ የድል ፡ ባለቤቶች

አዝ፦ ለእኔም ፡ ያንን ፡ ፀጋ ፡ በሕይወቴ ፡ አምቄ
በችግሬ ፡ ሰዓት ፡ ጌታዬን ፡ ጠብቄ
ልደርስ ፡ እወዳለሁ ፡ ወደዚያ ፡ ደረጃ
በሚሰጠኝ ፡ ጉልበት ፡ በእምነት ፡ እርምጃ

በቀደመው ፡ ትውልድ ፡ እሳት ፡ ነበር ፡ ልኩ
ለእምነት ፡ ትጋዳዮች ፡ የትግል ፡ መድረኩ
ለማይጠፋው ፡ ክብር ፡ ለሕያውም ፡ ተስፋ
ተዋግተው ፡ አልፈዋል ፡ በትልቅ ፡ ነቀፋ

አዝ፦ ለእኔም ፡ ያንን ፡ ፀጋ ፡ በሕይወቴ ፡ አምቄ
በችግሬ ፡ ሰዓት ፡ ጌታዬን ፡ ጠብቄ
ልደርስ ፡ እወዳለሁ ፡ ወደዚያ ፡ ደረጃ
በሚሰጠኝ ፡ ጉልበት ፡ በእምነት ፡ እርምጃ

አምላካቸው ፡ ከብሯል ፡ በአምልኮ ፡ ስግደት
በትልቅ ፡ ተጋድሎ ፡ በወንጌል ፡ ጤንነት
ከብረው ፡ አስከብረው ፡ የሕይወታቸውን ፡ ጌታ
ሊገናኙት ፡ ወጡ ፡ ያንን ፡ ባለ ፡ ውለታ

አዝ፦ ለእኔም ፡ ያንን ፡ ፀጋ ፡ በሕይወቴ ፡ አምቄ
በችግሬ ፡ ሰዓት ፡ ጌታዬን ፡ ጠብቄ
ልደርስ ፡ እወዳለሁ ፡ ወደዚያ ፡ ደረጃ
በሚሰጠኝ ፡ ጉልበት ፡ በእምነት ፡ እርምጃ

እኛም ፡ ተጠርተናል ፡ እንምሰል ፡ እነርሱን
የመከራን ፡ እሳት ፡ እንድናየው ፡ ልኩን
ስለዚህ ፡ ተጋደል ፡ የወንጌል ፡ አርበኛ
ሠይጣንን ፡ ግጠመው ፡ ያንተን ፡ ወደረኛ
ነው-ና- ፡ ድል ፡ የእኛ

አዝ፦ ለእኔም ፡ ያንን ፡ ፀጋ ፡ በሕይወቴ ፡ አምቄ
በችግሬ ፡ ሰዓት ፡ ጌታዬን ፡ ጠብቄ
ልደርስ ፡ እወዳለሁ ፡ ወደዚያ ፡ ደረጃ
በሚሰጠኝ ፡ ጉልበት ፡ በእምነት ፡ እርምጃ