ድል ፡ ለማድረግ ፡ ወጣ (Del Lemadreg Weta) - ተስፋዬ ፡ ጋቢሶ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ተስፋዬ ፡ ጋቢሶ
(Tesfaye Gabisso)

Tesfaye Gabisso Esp.jpg

ልዩ ፡ እትም
(Esp)

ምህረቱ ፡ አያልቅምና
(Meheretu Ayalqemena)

ቁጥር (Track):

(6)

ርዝመት (Len.): 2:26
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የተስፋዬ ፡ ጋቢሶ ፡ አልበሞች
(Albums by Tesfaye Gabisso)

የፈርዖን ፡ ገንዘብ ፡ ያልማረከው ፡ ጀግና
ዓይኑ ፡ ያልደከመ ፡ ያላለቀ ፡ ገና
ድል ፡ ለማድረግ ፡ ወጣ ፡ በጦርነት ፡ ሲቃ
በጀርባው ፡ አንግቦ ፡ የአምላኩን ፡ ጦር ፡ ዕቃ (፪x)

የወይኒው ፡ አስራት ፡ የግርፋት ፡ ብዛት
አልቻለው ፡ ሊያበርደው ፡ የፍቅሩን ፡ ትኩሳት
ፎከረ ፡ ያ ፡ ጐበዝ ፡ ሊጥል ፡ ሊገረስስ
ጠምዶ ፡ በቀኝ ፡ እጁ ፡ የቃሉን ፡ መትረየስ (፪x)

የልብ ፡ ዓይኑ ፡ ፈጦ ፡ ትኩር ፡ ብሎ ፡ እያየ
የጠላትን ፡ ምሽግ ፡ ሰፈሩን ፡ አጋዬ
የአርያም ፡ እሳት ፡ በኃይል ፡ ጐብኝቶታል
እባቡና ፡ ጊንጡን ፡ ከእግሩ ፡ ስር ፡ ረግጦታል (፪x)

በድካም ፡ በረታ ፡ ጅማቱ ፡ ጠንክሯል
አንገብግቦት ፡ ፍቅሩ ፡ ወኔው ፡ ተቀስቅሷል
በጀርባው ፡ መተልተል ፡ ጌታን ፡ አከበረ
የሞትንም ፡ ባሕር ፡ በእምነት ፡ ተሻገረ (፪x)