From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
|
ተስፋዬ ፡ ጋቢሶ (Tesfaye Gabisso)
|
|
ልዩ ፡ እትም (Esp)
|
አልበም (dsfsdf)
|
ዓ.ም. (Year):
|
፲ ፱ ፻ ፺ ፭ (1980)
|
ቁጥር (Track):
|
፲ ፬ (14)
|
ርዝመት (Len.):
|
3:10
|
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች (Other Songs in the Album)
|
|
የተስፋዬ ፡ ጋቢሶ ፡ አልበሞች (Albums by Tesfaye Gabisso)
|
|
ከምድር ፡ በላይ ፡ ቢሆን ፡ ከሰማይም ፡ በታች
መግባት ፡ መውጣታችን ፡ ዘወትር ፡ ተመልካች
እንደ ፡ ኢየሱስ ፡ ያለ ፡ ማንን ፡ አገኛችሁ
የሕይወት ፡ ዋስትና ፡ ጌታ ፡ ሚሆናችሁ
አዝ፦ በእምነት ፡ እኖራለሁ ፡ ጌታዬን ፡ አውቃለሁ
የእኔን ፅኑ አምባ ፡ ተተግኜዋለው
ወጀቡን ፡ ሳልፈራ ፡ ታግዬ ፡ እረታለሁ
የክብር ፡ ሽልማቴን ፡ ከእጁ ፡ እረከባለሁ
ለነገ ፡ አይጨንቀኝም ፡ ጭጋግ ፡ ቢሸፍነው
ወይኑ ፡ ቢጠወልግ ፡ ሃሩሩ ፡ ቢያሰጋው
ለእግሬ ፡ መብራት ፡ ነው ፡ ቃሉ ፡ በእጄ ፡ ያለው
የተፈጥሮ ፡ አዛዥ ፡ ኢየሱስ ፡ ሕያው ፡ ነው
አዝ፦ በእምነት ፡ እኖራለሁ ፡ ጌታዬን ፡ አውቃለሁ
የእኔን ፡ ፅኑ ፡ አምባ ፡ ተተግኜዋለው
ወጀቡን ፡ ሳልፈራ ፡ ታግዬ ፡ እረታለሁ
የክብር ፡ ሽልማቴን ፡ ከእጁ ፡ እረከባለሁ
ፈቃዱ ፡ ሲሞላ ፡ ጌታዬ ፡ ከብሮ ፡ ሳይ
ምድር ፡ ዕልል ፡ ስትል ፡ ስያጨበጭብ: ፡ ሰማይ
መጠለያ ፡ ልብሴ ፡ እንጀራየ ፡ ያ ፡ ነው
ነፍሴ ፡ ትጠግባለች ፡ በክብር ፡ በግርማው
አዝ፦ በእምነት ፡ እኖራለሁ ፡ ጌታዬን ፡ አውቃለሁ
የእኔን ፅኑ አምባ ፡ ተተግኜዋለው
ወጀቡን ፡ ሳልፈራ ፡ ታግዬ ፡ እረታለሁ
የክብር ፡ ሽልማቴን ፡ ከእጁ ፡ እረከባለሁ
|