የእኔ ፡ ጌታ (Yenie Gieta) - ተስፋዬ ፡ ጋቢሶ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ተስፋዬ ፡ ጋቢሶ
(Tesfaye Gabisso)

Lyrics.jpg


(2)

እግዚአብሔር ፡ መንፈስ ፡ ነው
(Egziabhier Menfes New)

ቁጥር (Track):

፲ ፩ (11)

ርዝመት (Len.): 4:13
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የተስፋዬ ፡ ጋቢሶ ፡ አልበሞች
(Albums by Tesfaye Gabisso)

ጌቴ ፡ ኢየሱስ ፡ የእኔ ፡ ቤዛ
ጉስቁልናዬ ፡ ቢበዛ
ከክብሩ ፡ ተዋረደልኝ
በእኔ ፡ ፈንታ ፡ ታረደልኝ (፪x)

አዝ፦ የእኔ ፡ ጌታ ፡ ስለ ፡ እኔ ፡ ገዶት
ኃጢአቴም ፡ አስጨንቆት
ዝም ፡ ብሎ ፡ እንደ ፡ ጠቦት
በሀሰት ፡ ተመስክሮበት ፡ በችሎት
ዕዳዬን ፡ ከፍሎታል ፡ ተሰቅሎ ፡ በመሞት

ግብዝ ፡ አይደል ፡ እንደ ፡ ሰው
ወረት ፡ ጨርሶ ፡ ያልነካው
በጐልጐታ ፡ ላይ ፡ የታየው
እውነትም ፡ እርሱ ፡ ፍቅር ፡ ነው (፪x)

አዝ፦ የእኔ ፡ ጌታ ፡ ስለ ፡ እኔ ፡ ገዶት
ኃጢአቴም ፡ አስጨንቆት
ዝም ፡ ብሎ ፡ እንደ ፡ ጠቦት
በሀሰት ፡ ተመስክሮበት ፡ በችሎት
ዕዳዬን ፡ ከፍሎታል ፡ ተሰቅሎ ፡ በመሞት

ያጀቡት ፡ ሁሉ ፡ ፈርጥጠው
ለሰይፍ ፡ ለጐመድ ፡ አጋልጠው
በዚያን ፡ ምሽት ፡ አልቦታል
ቃቶ ፡ ነፍሴን ፡ ታድጓታል (፪x)

አዝ፦ የእኔ ፡ ጌታ ፡ ስለ ፡ እኔ ፡ ገዶት
ኃጢአቴም ፡ አስጨንቆት
ዝም ፡ ብሎ ፡ እንደ ፡ ጠቦት
በሀሰት ፡ ተመስክሮበት ፡ በችሎት
ዕዳዬን ፡ ከፍሎታል ፡ ተሰቅሎ ፡ በመሞት

በግፍ ፡ ጀርባው ፡ ተላልጦ
እግሩንም ፡ ለስቃይ ፡ ገልጦ
ንጹስህ ፡ ደሙን ፡ ለእኔ ፡ ከፍሎ
በቀራንዮ ፡ ደርቆ ፡ ውሎ (፪x)

አዝ፦ የእኔ ፡ ጌታ ፡ ስለ ፡ እኔ ፡ ገዶት
ኃጢአቴም ፡ አስጨንቆት
ዝም ፡ ብሎ ፡ እንደ ፡ ጠቦት
በሀሰት ፡ ተመስክሮበት ፡ በችሎት
ዕዳዬን ፡ ከፍሎታል ፡ ተሰቅሎ ፡ በመሞት

ይህ ፡ ፍቅር ፡ በሕይወቴ ፡ ገብቶ
የደህንነት ፡ ሥራ ፡ ሰርቶ
ቆሻሻነቴን ፡ ቀይሮ
አይቻለሁኝ ፡ ውብ ፡ ኑሮ (፪x)

አዝ፦ የእኔ ፡ ጌታ ፡ ስለ ፡ እኔ ፡ ገዶት
ኃጢአቴም ፡ አስጨንቆት
ዝም ፡ ብሎ ፡ እንደ ፡ ጠቦት
በሀሰት ፡ ተመስክሮበት ፡ በችሎት
ዕዳዬን ፡ ከፍሎታል ፡ ተሰቅሎ ፡ በመሞት