አስብበት (Asebebet) - ተስፋዬ ፡ ጋቢሶ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ተስፋዬ ፡ ጋቢሶ
(Tesfaye Gabisso)

Lyrics.jpg


(2)

እግዚአብሔር ፡ መንፈስ ፡ ነው
(Egziabhier Menfes New)

ቁጥር (Track):

(2)

ርዝመት (Len.): 3:21
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የተስፋዬ ፡ ጋቢሶ ፡ አልበሞች
(Albums by Tesfaye Gabisso)

የፀጋ ፡ የምህረት ፡ ዘመኑ ፡ አብቅቶ
ብርሃን ፡ ተሰውሮ ፡ የጥሪው ፡ ቀን ፡ መሽቶ
ሰማያት ፡ ተፈተው ፡ ምድር ፡ ሳትናውጥ
በነበልባል ፡ እሳት ፡ ጌታም ፡ ሳይገለጥ

አዝ፦ አስብበት ፡ ዛሬ ፡ ነገን ፡ አትጠብቅ
ራስህን ፡ ስትደልል ፡ ዘመንህም ፡ አይለቅ
ሕይወት ፡ ኢየሱስ ፡ ነው ፡ ሌላስ ፡ አታገኝም
አምነህ ፡ ድነህበት ፡ ታተም ፡ ለዘለዓለም

አብሮ ፡ ደስ ፡ ይበለን ፡ ትንሽ ፡ ቆይ ፡ ስትልህ
ዓለም ፡ በለዘብታ ፡ እያባበለችህ
ተደላ ፡ ትካዜና ፡ ቁጭትን ፡ ጠብቆ
ሲዖል ፡ እንዳትገባ ፡ ሳታስበው ፡ ከቶ

አዝ፦ አስብበት ፡ ዛሬ ፡ ነገን ፡ አትጠብቅ
ራስህን ፡ ስትደልል ፡ ዘመንህም ፡ አይለቅ
ሕይወት ፡ ኢየሱስ ፡ ነው ፡ ሌላስ ፡ አታገኝም
አምነህ ፡ ድነህበት ፡ ታተም ፡ ለዘለዓለም

የእግዚአብሔር ፡ ነገር ፡ ለፍጥረታዊ ፡ ሰው
ሊገባው ፡ አይችልም ፡ ፍፁም ፡ ሞኝነት ፡ ነው
ፍጥረታዊውን ፡ ሥጋ ፡ መንፈሱ ፡ ሲሽረው
ያኔ ፡ ትረዳለህ ፡ መንገዱ ፡ ጥበብ ፡ ነው

አዝ፦ አስብበት ፡ ዛሬ ፡ ነገን ፡ አትጠብቅ
ራስህን ፡ ስትደልል ፡ ዘመንህም ፡ አይለቅ
ሕይወት ፡ ኢየሱስ ፡ ነው ፡ ሌላስ ፡ አታገኝም
አምነህ ፡ ድነህበት ፡ ታተም ፡ ለዘለዓለም

በመንታ ፡ መንገድ ፡ ላይ ፡ ሆነህ ፡ ስታማርጥ
ፈጽሞ ፡ ላትረካ ፡ መንገድ ፡ ስትለዋውጥ
ሞት ፡ ጥላውን ፡ ጥሎ ፡ አፍኖ ፡ ሳይወስድህ
ጌታን ፡ ተቀበለው ፡ እርሱ ፡ ነው ፡ የሚያረካህ

አዝ፦ አስብበት ፡ ዛሬ ፡ ነገን ፡ አትጠብቅ
ራስህን ፡ ስትደልል ፡ ዘመንህም ፡ አይለቅ
ሕይወት ፡ ኢየሱስ ፡ ነው ፡ ሌላስ ፡ አታገኝም
አምነህ ፡ ድነህበት ፡ ታተም ፡ ለዘለዓለም