ለእኔም ፡ አባቴ ፡ ሆይ (Leniem Abatie Hoy) - ተስፋዬ ፡ ጋቢሶ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ተስፋዬ ፡ ጋቢሶ
(Tesfaye Gabisso)

Lyrics.jpg


(1)

እግዚአብሔር ፡ ኃያል
(Egziabhier Hayal)

ቁጥር (Track):

(1)

ርዝመት (Len.): 4:00
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የተስፋዬ ፡ ጋቢሶ ፡ አልበሞች
(Albums by Tesfaye Gabisso)

መዋረዳቸውን ፡ አይተህ ፡ አንተ ፡ ባርከሃቸው
የቤትህን ፡ ልጆች ፡ አንተ ፡ ሰብረሃቸው
ትዕቢታቸው ፡ ቀርቶ ፡ በትሁት ፡ ልባቸው
እንባቸውን ፡ ሲያፈሱት ፡ ለአንተ ፡ አየኋቸው

አዝ፦ ለእኔም ፡ አባቴ ፡ ሆይ ፡ ልቤን ፡ ስበርልኝ
እኔነቴ ፡ ቅርቶ ፡ ጸጋህ ፡ እንዲበዛልኝ
ትዕቢቴን ፡ ሽረህ ፡ ትህትና ፡ አልብሰኝ (፪x)

ጌታ ፡ ዘወትር ፡ መሰበርን ፡ ሽቼ
አብዝቼ ፡ እጮሃለሁ ፡ ሌተቀን ፡ ተግቼ
እስከመቸ ፡ ድረስ ፡ ሕይወቴ ፡ እንዲህ ፡ ደርቆ
እኖራለሁ ፡ ጌታ ፡ ልምላሜ ፡ አርጐ

አዝ፦ ለእኔም ፡ አባቴ ፡ ሆይ ፡ ልቤን ፡ ስበርልኝ
እኔነቴ ፡ ቅርቶ ፡ ጸጋህ ፡ እንዲበዛልኝ
ትዕቢቴን ፡ ሽረህ ፡ ትህትና ፡ አልብሰኝ (፪x)

የመሰበር ፡ ፍላጐቴ ፡ ግለቱ ፡ ሳይበርድ
ሰማዬችን ፡ ከፍተህ ፡ ምነው ፡ ብትወርድ
ምርኩዜን ፡ ፈትነህ ፡ እባክህ ፡ ስበረኝ
ትሁትና ፡ ታዛዥ ፡ መሆን ፡ አስተምረኝ

አዝ፦ ለእኔም ፡ አባቴ ፡ ሆይ ፡ ልቤን ፡ ስበርልኝ
እኔነቴ ፡ ቅርቶ ፡ ጸጋህ ፡ እንዲበዛልኝ
ትዕቢቴን ፡ ሽረህ ፡ ትህትና ፡ አልብሰኝ (፪x)

የራሴን ፡ ማንነት ፡ ያኔ ፡ በርግጥ ፡ እረዳለሁ
የውስጥ ፡ ዓይኔ ፡ በርቶ ፡ አብዝቼም ፡ አያለሁ
በፍፁም ፡ ግልጽነት ፡ ስምህን ፡ አውጃለሁ
በበረከት ፡ ሙላት ፡ አስከብርሃለሁ

አዝ፦ ለእኔም ፡ አባቴ ፡ ሆይ ፡ ልቤን ፡ ስበርልኝ
እኔነቴ ፡ ቅርቶ ፡ ጸጋህ ፡ እንዲበዛልኝ
ትዕቢቴን ፡ ሽረህ ፡ ትህትና ፡ አልብሰኝ (፪x)