From WikiMezmur: Mezmur Lyrics
-- 72.185.227.148 16:51, 12 ሜይ 2020 (UTC)
አዝ፦ ኃጢአት ፡ ሥሩን ፡ ሰዶ ፡ ሳይጠነክርብኝ
ሳይታወቀኝ ፡ አድጐ ፡ ሞትን ፡ ሳይወልድብኝ
ንስሃ ፡ እንደገባ ፡ በጊዜ ፡ ገስፀኝ (፪x)
የሌብነት ፡ ካባ ፡ ወርቁም ፡ ሆነ ፡ ብሩ
ከድንኳኔ ፡ በታች ፡ ተቀብረው ፡ ሳይቀሩ
ቃልህን ፡ ለመጠበቅ ፡ ልጆችህ ፡ ሲጥሩ
በተደበቀ ፡ እርም ፡ ወድቀው ፡ ሲማረሩ
አዝ፦ ኃጢአት ፡ ሥሩን ፡ ሰዶ ፡ ሳይጠነክርብኝ
ሳይታወቀኝ ፡ አድጐ ፡ ሞትን ፡ ሳይወልድብኝ
ንስሃ ፡ እንደገባ ፡ በጊዜ ፡ ገስፀኝ (፪x)
ኃጢአትን ፡ ታቅ--~~~~ፌ ፡ ጌታ ፡ ሆይ ፡ ብልህም
ውስጤ ፡ ሳይስተካከል ፡ ብዘምርልህም
ወይም ፡ ብሰብክልህ ፡ ጉድለቴን ፡ ሳላውቀው
ምን ፡ ፍሬ ፡ ይገኛል ፡ በከንቱ ፡ መሮጥ ፡ ነው
አዝ፦ ኃጢአት ፡ ሥሩን ፡ ሰዶ ፡ ሳይጠነክርብኝ
ሳይታወቀኝ ፡ አድጐ ፡ ሞትን ፡ ሳይወልድብኝ
ንስሃ ፡ እንደገባ ፡ በጊዜ ፡ ገስፀኝ (፪x)
ጌታ ፡ ሆይ ፡ የለኝም ፡ ከአንተ ፡ የሚቀርበኝ
ድካሜን ፡ ብርታቴን ፡ ተረድቶ ፡ የሚያውቅልኝ
ስለዚህ ፡ መርምረህ ፡ ንገረኝ ፡ በደሌን
ንስሃ ፡ ልግባ ፡ እኔ ፡ አዋርጄ ፡ እራሴን
አዝ፦ ኃጢአት ፡ ሥሩን ፡ ሰዶ ፡ ሳይጠነክርብኝ
ሳይታወቀኝ ፡ አድጐ ፡ ሞትን ፡ ሳይወልድብኝ
ንስሃ ፡ እንደገባ ፡ በጊዜ ፡ ገስፀኝ (፪x)
|