በጊዜውም ፡ አለጊዜውም (Begiziewem Alegiziewem) - ተስፋዬ ፡ ጋቢሶ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ተስፋዬ ፡ ጋቢሶ
(Tesfaye Gabisso)

Lyrics.jpg


(1)

እግዚአብሔር ፡ ኃያል
(Egziabhier Hayal)

ቁጥር (Track):

(8)

ርዝመት (Len.): 4:09
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የተስፋዬ ፡ ጋቢሶ ፡ አልበሞች
(Albums by Tesfaye Gabisso)

የጠላቴን ፡ እራስ ፡ ቀጥቅጠህ ፡ ከመጋጋው ፡ እኔን ፡ ነጥቀህ
ቅዱስ ፡ ደምህን ፡ አፍስሰህ ፡ ለሙት ፡ ልጅህ ፡ ሕይወት ፡ ሰጥተህ
ታላቁን ፡ መዳን፡ ድኛለሁ ፡ አሁንም ፡ መጽናት፡ አሻለሁ

አዝ፦ በጊዜውም ፡ አለጊዜውም ፡ በስምህ: ጸንቼ : ቆሜ
ፊትህን ፡ ለማየት ፡ እጓጓለሁ ፡ እሩጫዬን ፡ ፈጽሜ
ስለዚህ ፡ ፈቃድህን ፡ ይሁንልኝ ፡ ውድ ፡ አባቴ
በሰላም ፡ በጤና ፡ አድርሰኝ ፡ ከቤቴ

ስቅበዘበዝ ፡ መክረኸኛል ፡ ስተክዝ ፡ አፅናንተኸኛል
ባቆስልህም ፡ ወደኸኛል ፡ ዘወትር ፡ ተሸክመኸኛል
እስከዛሬ ፡ ችለኸኛል ፡ ቅዱስ ፡ ሥምህ ፡ አቁሞኛል

አዝ፦ በጊዜውም ፡ አለጊዜውም ፡ በስምህ፡ ፀንቼ ፡ ቆሜ
ፊትህን ፡ ለማየት ፡ እጓጓለሁ ፡ እሩጫዬን ፡ ፈጽሜ
ስለዚህ ፡ ፈቃድህን ፡ ይሁንልኝ ፡ ውድ ፡ አባቴ
በሰላም ፡ በጤና ፡ አድርሰኝ ፡ ከቤቴ

ዘወትር ፡ በሁሉም ፡ ስፍራ ፡ አንተን ፡ ልምሰል ፡ አንተን ፡ ልፍራ
ከዓለም ፡ አድርገኝ ፡ ልዩ ፡ በእኔም ፡ ሕይወት ፡ አንተን ፡ ይዩ
ሥጋዬን ፡ ለዓለም ፡ ሰቅዬ ፡ ልጓዝ ፡ አንተን ፡ ተከትዬ

አዝ፦ በጊዜውም ፡ አለጊዜውም ፡ በስምህ፡ ፀንቼ ፡ ቆሜ
ፊትህን ፡ ለማየት ፡ እጓጓለሁ ፡ እሩጫዬን ፡ ፈጽሜ
ስለዚህ ፡ ፈቃድህን ፡ ይሁንልኝ ፡ ውድ ፡ አባቴ
በሰላም ፡ በጤና ፡ አድርሰኝ ፡ ከቤቴ

በድካም ፡ ሕይወቴ ፡ ላልቶ ፡ አካሄዴም ፡ ተበላሽቶ
ቅዱስ ፡ ሥምህ ፡ አንዳይሰደብ ፡ አደራ ፡ ልጅህን ፡ አስብ
እስክትመጣልኝ ፡ በክብር ፡ አንተን ፡ አስከብሬ ፡ ልኑር

አዝ፦ በጊዜውም ፡ አለጊዜውም ፡ በስምህ፡ ፀንቼ ፡ ቆሜ
ፊትህን ፡ ለማየት ፡ እጓጓለሁ ፡ እሩጫዬን ፡ ፈጽሜ
ስለዚህ ፡ ፈቃድህን ፡ ይሁንልኝ ፡ ውድ ፡ አባቴ
በሰላም ፡ በጤና ፡ አድርሰኝ ፡ ከቤቴ

በከፍታም ፡ በዝቅታም ፡ በሀዘንም ፡ በደስታም
ሳልደናገር ፡ በእርጋታ ፡ በፈተናም ፡ ሳልረታ
በትጋት ፡ ፀንቼ ፡ በእምነት ፡ ፊትህን ፡ ልየው ፡ በክበር

አዝ፦ በጊዜውም ፡ አለጊዜውም ፡ በስምህ፡ ፀንቼ ፡ ቆሜ
ፊትህን ፡ ለማየት ፡ እጓጓለሁ ፡ እሩጫዬን ፡ ፈጽሜ
ስለዚህ ፡ ፈቃድህን ፡ ይሁንልኝ ፡ ውድ ፡ አባቴ
በሰላም ፡ በጤና ፡ አድርሰኝ ፡ ከቤቴ