From WikiMezmur: Mezmur Lyrics
አዝ፦ ያ ፡ ተከራታቹ ፡ ኮብላይ ፡ ወገናችን
መቷል ፡ እንደገና ፡ እሰይ ፡ ደስ ፡ ይበለን
ያ ፡ ተከራታቹ ፡ ኮብላይ ፡ ወገናችን
መቷል ፡ እንደገና ፡ እሰይ ፡ ደስ ፡ ይበለን (፪x)
በመዳኑ ፡ ምክንያት ፡ መላዕክት ፡ ፈንጭተው
በአገልግሎቱም ፡ ብዙ ፡ ሰዎች ፡ ረክተው
ያንን ፡ ሰው ፡ በቃሉ ፡ እንቅፋት ፡ እግኝቶት
ወድቆ ፡ የነበረው ፡ አዳኙንም ፡ ከድቶ
አዝ፦ ያ ፡ ተከራታቹ ፡ ኮብላይ ፡ ወገናችን
መቷል ፡ እንደገና ፡ እሰይ ፡ ደስ ፡ ይበለን
ያ ፡ ተከራታቹ ፡ ኮብላይ ፡ ወገናችን
መቷል ፡ እንደገና ፡ እሰይ ፡ ደስ ፡ ይበለን (፪x)
መርዶውን ፡ እየሰሙ ፡ ሰዎች ፡ አልቅሰውለት
ጌታ ፡ እንዲያስነሳው ፡ ከልብ ፡ ጸልየውለት
በመራራ ፡ ጩሕ ፡ ፡ ት ፡ ለአምላኩ ፡ ነግረውለት
መልሶ ፡ እምጥቶታል ፡ እግዚአብሔር ፡ አዝኖለት
አዝ፦ ያ ፡ ተከራታቹ ፡ ኮብላይ ፡ ወገናችን
መቷል ፡ እንደገና ፡ እሰይ ፡ ደስ ፡ ይበለን
ያ ፡ ተከራታቹ ፡ ኮብላይ ፡ ወገናችን
መቷል ፡ እንደገና ፡ እሰይ ፡ ደስ ፡ ይበለን (፪x)
የውድቀቱን ፡ ምክንያት ፡ ነግሮ ፡ አስጠንቅቆታል
ወንድሞቹ ፡ ቀድሞ ፡ ጌታ ፡ አምጥቶለታል
ተስፋን ፡ እየናቀም ፡ በወጥመድ ፡ ቢገባም
ጌታ ፡ ቸር ፡ ነውና ፡ አይጨክንበትም
አዝ፦ ያ ፡ ተከራታቹ ፡ ኮብላይ ፡ ወገናችን
መቷል ፡ እንደገና ፡ እሰይ ፡ ደስ ፡ ይበለን
ያ ፡ ተከራታቹ ፡ ኮብላይ ፡ ወገናችን
መቷል ፡ እንደገና ፡ እሰይ ፡ ደስ ፡ ይበለን (፪x)
ያን ፡ ጨካኝ ፡ አንበሳ ፡ በግልጽ ፡ አስፍሮ
በብረቱ ፡ በትር ፡ መንጋጋውን ፡ ሰብሮ
ዳግም ፡ አምጥቶታል ፡ እግዚአብሔር ፡ ይመስገን
ሙሾው ፡ ተለውጧል ፡ እሰይ ፡ ደስ ፡ ይበለን
አዝ፦ ያ ፡ ተከራታቹ ፡ ኮብላይ ፡ ወገናችን
መቷል ፡ እንደገና ፡ እሰይ ፡ ደስ ፡ ይበለን
ያ ፡ ተከራታቹ ፡ ኮብላይ ፡ ወገናችን
መቷል ፡ እንደገና ፡ እሰይ ፡ ደስ ፡ ይበለን (፪x)
|