ጠላቴ ፡ ሆይ (Telatie Hoy) - ተስፋዬ ፡ ጋቢሶ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ተስፋዬ ፡ ጋቢሶ
(Tesfaye Gabisso)

Lyrics.jpg


(3)

ክርስቲያን ፡ ተሻገረ
(Christian Teshagere)

ቁጥር (Track):

፲ ፪ (12)

ርዝመት (Len.): 3:24
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የተስፋዬ ፡ ጋቢሶ ፡ አልበሞች
(Albums by Tesfaye Gabisso)

አዝ፦ ጠላቴ ፡ ሆይ ፡ ብወድቅ ፡ እነሳለሁኝ
በጨለማ ፡ ብቀመጥ ፡ እንኳን
እግዚአብሔር ፡ ብርሃን ፡ ይሆንልኛል
ስለዚህ ፡ ስለዚህ ፡ በእኔ ፡ ደስ ፡ አይበልህ

የወይኑ ፡ ፍሬ ፡ ተለቅሞ ፡ እንደቀረው ፡ ቃርሚያ
ደርቄ ፡ ቆሜያለሁ ፡ እኔ ፡ ከበረከት ፡ በስቲያ
የሃዘን ፡ እንጉርጉሮዬን ፡ የምሬት ፡ ለቅሶዬን
በአምላኬ ፡ ፊት ፡ እለቃለሁ ፡ እንዲያያት ፡ ሕይወቴን

አዝ፦ ጠላቴ ፡ ሆይ ፡ ብወድቅ ፡ እነሳለሁኝ
በጨለማ ፡ ብቀመጥ ፡ እንኳን
እግዚአብሔር ፡ ብርሃን ፡ ይሆንልኛል
ስለዚህ ፡ ስለዚህ ፡ በእኔ ፡ ደስ ፡ አይበልህ

በእግዚአብሔር ፡ ላይ ፡ ኃጥያትን ፡ ሰርቻለሁና
ቁጣው ፡ ለቅጣቴ ፡ ሆኖ ፡ ነዶብኛልና
ወደ ፡ ብርሃን ፡ እስኪያወጣኝ ፡ እታገሳለሁኝ
መልሶም ፡ እስኪምረኝ ፡ ድረሰ ፡ ጠብቀዋለሁኝ

አዝ፦ ጠላቴ ፡ ሆይ ፡ ብወድቅ ፡ እነሳለሁኝ
በጨለማ ፡ ብቀመጥ ፡ እንኳን
እግዚአብሔር ፡ ብርሃን ፡ ይሆንልኛል
ስለዚህ ፡ ስለዚህ ፡ በእኔ ፡ ደስ ፡ አይበልህ

በእኔና ፡ በአምላኬ ፡ መሃል ፡ የሚኖረውን ፡ ጉዳይ
ኢየሱስ ፡ ይፈፅመዋል ፡ የመሰረቱ ፡ ድንጋይ
ስለዚህ ፡ ጠላቴ ፡ ወግድ ፡ ጌታ ፡ ይገስጽህ
አሁንም ፡ ቢሆን ፡ ልጁ ፡ ነኝ ፡ ተረዳ ፡ ከልብህ

አዝ፦ ጠላቴ ፡ ሆይ ፡ ብወድቅ ፡ እነሳለሁኝ
በጨለማ ፡ ብቀመጥ ፡ እንኳን
እግዚአብሔር ፡ ብርሃን ፡ ይሆንልኛል
ስለዚህ ፡ ስለዚህ ፡ በእኔ ፡ ደስ ፡ አይበልህ

ለዘለዓለም ፡ አይቆጣም ፡ ምህረትን ፡ ይወዳል
የጠላቴን ፡ ምኞት ፡ ቆርጦ ፡ ዕልልታውን፡ ያቆማል
የውርደት ፡ ማቄ ፡ ተቀዶ ፡ ነጭ ፡ ልብስ ፡ ለብሼ
ዳግም ፡ ዘምራለሁ ፡ ለእርሱ ፡ ክንዱን ፡ ተንተርሼ

አዝ፦ ጠላቴ ፡ ሆይ ፡ ብወድቅ ፡ እነሳለሁኝ
በጨለማ ፡ ብቀመጥ ፡ እንኳን
እግዚአብሔር ፡ ብርሃን ፡ ይሆንልኛል
ስለዚህ ፡ ስለዚህ ፡ በእኔ ፡ ደስ ፡ አይበልህ