በትዕግሥት ፡ ፀጥታ (Betegest Tseteta) - ተስፋዬ ፡ ጋቢሶ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ተስፋዬ ፡ ጋቢሶ
(Tesfaye Gabisso)

Lyrics.jpg


(3)

ክርስቲያን ፡ ተሻገረ
(Christian Teshagere)

ቁጥር (Track):

(3)

ርዝመት (Len.): 3:13
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የተስፋዬ ፡ ጋቢሶ ፡ አልበሞች
(Albums by Tesfaye Gabisso)

አዝ፦ በትዕግሥት ፡ ፀጥታ ፡ በፀሎት ፡ ቆይታ
ድል ፡ ይገኛል ፡ ከጌታ
በትዕግሥት ፡ ፀጥታ ፡ በፀሎት ፡ ቆይታ
መልስ ፡ ይመጣል ፡ ከጌታ

የበረታ ፡ ሰልፍ ፡ ሲከበኝ ፡ ከኋላ ፡ ከፊት
ቆይቼ ፡ እግዚአብሔርን ፡ ደጅ ፡ ጠናሁት
እርሱም ፡ ዘንበል ፡ አለልኝ ፡ ሊያዳምጠኝ
እንባዬን ፡ በእጁ ፡ ጠርጐ ፡ ቃሉን ፡ ሰጥቶ ፡ አፅናናኝ

አዝ፦ በትዕግሥት ፡ ፀጥታ ፡ በፀሎት ፡ ቆይታ
ድል ፡ ይገኛል ፡ ከጌታ
በትዕግሥት ፡ ፀጥታ ፡ በፀሎት ፡ ቆይታ
መልስ ፡ ይመጣል ፡ ከጌታ

ነፍስህ ፡ ብትራቆት ፡ ፍፁም ፡ ባዶ ፡ ስትሆን
ያለህን ፡ አራግፈህ ፡ ተዘርፈህ ፡ ስታይ ፡ ራስህን
ያሳለፍካቸውን ፡ ድሎች ፡ አስብ ፡ ተስፋህ ፡ ይለምልም
ተንበርክከህ ፡ ብትቆይ ፡ ደግሞ ፡ መዳሰስህ ፡ አይቀርም

አዝ፦ በትዕግሥት ፡ ፀጥታ ፡ በፀሎት ፡ ቆይታ
ድል ፡ ይገኛል ፡ ከጌታ
በትዕግሥት ፡ ፀጥታ ፡ በፀሎት ፡ ቆይታ
መልስ ፡ ይመጣል ፡ ከጌታ

ከድካም ፡ የበረቱ ፡ ሰዎች ፡ በድል ፡ ያለፉ
ከኢየሱስ ፡ በስተቀኝ ፡ በላይ ፡ የተሰለፉ
መንግሥታትን ፡ ድል ፡ ነስተው ፡ ያንን ፡ ምሽግ ፡ የናዱ
የፀሎት ፡ ሰዎች ፡ ናቸው ፡ ጠላት ፡ ያርበተበዱ

አዝ፦ በትዕግሥት ፡ ፀጥታ ፡ በፀሎት ፡ ቆይታ
ድል ፡ ይገኛል ፡ ከጌታ
በትዕግሥት ፡ ፀጥታ ፡ በፀሎት ፡ ቆይታ
መልስ ፡ ይመጣል ፡ ከጌታ