አንተ ፡ ግን ፡ ጌታ ፡ ሆይ (Ante Gen Gieta Hoy) - ተስፋዬ ፡ ጋቢሶ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ተስፋዬ ፡ ጋቢሶ
(Tesfaye Gabisso)

Lyrics.jpg


(3)

ክርስቲያን ፡ ተሻገረ
(Christian Teshagere)

ቁጥር (Track):

፲ ፭ (15)

ርዝመት (Len.): 3:29
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የተስፋዬ ፡ ጋቢሶ ፡ አልበሞች
(Albums by Tesfaye Gabisso)

በተዘረጋ ፡ ክንድ ፡ በበረታችም ፡ እጅ
በጌታ ፡ መዳኑን ፡ ከሞት ፡ ከሲዖል ፡ እጅ
እንደምን ፡ ዘንግቶ ፡ ሰው ፡ ያጉረመርማል
ወንድሙን ፡ ለመውገር ፡ እጁን ፡ ይዘረጋል

አዝ፦ ስጋ ፡ ነፍሱን ፡ ዘርቶ ፡ አመጽ ፡ አቆጥቁጦ
ትህትና ፡ ተረስቶ ፡ የትዕቢት ፡ ኃይል ፡ ፈጦ
ፍቅርን ፡ ገደል ፡ ከቶ ፡ ጥላቻን ፡ ለማንገሥ
ጥርሱን ፡ ይስል ፡ ጀመር ፡ ሰው ፡ ለመነካከስ
አንተ ፡ ግን ፡ ጌታ ፡ ሆይ ፡ ምህረትህን ፡ አፍስስ (፪x)

ስፍራውን ፡ ለቆ ፡ ሲሄድ ፡ ለመጉደፍ ፡ ሲቸኩል
ትህትናውን ፡ አውልቆ ፡ ለሞት ፡ ሲንቀለቀል
እዪት ፡ ያንን ፡ ዝንጉ ፡ ቃል ፡ ኪዳኑን ፡ ሲያፈርስ
በአመጻው ፡ ብዛት ፡ ፍቅርን ፡ ሲያቀዘቅዝ

አዝ፦ ስጋ ፡ ነፍሱን ፡ ዘርቶ ፡ አመጽ ፡ አቆጥቁጦ
ትህትና ፡ ተረስቶ ፡ የትዕቢት ፡ ኃይል ፡ ፈጦ
ፍቅርን ፡ ገደል ፡ ከቶ ፡ ጥላቻን ፡ ለማንገሥ
ጥፍሩን ፡ ይስል ፡ ጀመር ፡ ሰው ፡ ለመነካከስ
አንተ ፡ ግን ፡ ጌታ ፡ ሆይ ፡ ምህረትህን ፡ አፍስስ (፪x)

አንተን ፡ እየፈራሁ ፡ ቀኑን ፡ ሁሉ ፡ ልኑር
ትህትናም ፡ አይራቀኝ ፡ አልነፈግህ ፡ ክብር
እጅህ ፡ እንዳይመታኝ ፡ አጉል ፡ ደፋር ፡ ሆኜ
መተረቻ ፡ እንዳልሆን ፡ በሃፍረት ፡ ተከድኜ

አዝ፦ ስጋ ፡ ነፍሱን ፡ ዘርቶ ፡ አመጽ ፡ አቆጥቁጦ
ትህትና ፡ ተረስቶ ፡ የትዕቢት ፡ ኃይል ፡ ፈጦ
ፍቅርን ፡ ገደል ፡ ከቶ ፡ ጥላቻን ፡ ለማንገሥ
ጥፍሩን ፡ ይስል ፡ ጀመር ፡ ሰው ፡ ለመነካከስ
አንተ ፡ ግን ፡ ጌታ ፡ ሆይ ፡ ምህረትህን ፡ አፍስስ (፪x)