ክብር ፡ ለኢየሱስ ፡ ይሁን (Keber Leyesus Yehun) - ተስፋዬ ፡ ጋቢሶ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ተስፋዬ ፡ ጋቢሶ
(Tesfaye Gabisso)

Lyrics.jpg


(10)

አዎን ፡ ይሆናል
(Awon Yehonal)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፬ (2012)
ቁጥር (Track):

(7)

ርዝመት (Len.): 4:45
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የተስፋዬ ፡ ጋቢሶ ፡ አልበሞች
(Albums by Tesfaye Gabisso)

በቀራንዮ ፡ መስቀል ፡ ላይ ፡ በደዌ ፡ የደቀቀው
ነፍሱን ፡ ስለ ፡ ኃጥያቴ ፡ መስዋዕት ፡ ያደረገው
የሞትን ፡ ቀንበር ፡ ሰብሮ ፡ እኔኑ ፡ ሊያወጣ ፡ ነው
ማዳኑን ፡ ቀምሻለው ፡ ምን ፡ አለ ፡ የምመልሰው (፪x)

አዝ፦ ክብር ፡ ለኢየሱስ ፡ ይሁን
አየን ፡ አሸናፊነቱን
ኃያል ፡ እንደ ፡ እርሱ ፡ የለም
ይንገሥ ፡ ለዘለዓለም (፪x)

የተናቀ ፡ ደካማ ፡ ቢመስልም ፡ አመጣጡ
ከእሰይ ፡ ልጅ ፡ ከዳዊት ፡ ሥር ፡ የወጣው ፡ ቁጥቋጡ
ኢየሱስ ፡ አሸነፈ ፡ ፍሬው ፡ ምድርን ፡ ሸፈነ
የእግዚአብሔር ፡ ፈቃድ ፡ በእጁ ፡ ተከናወነ (፪x)

አዝ፦ ክብር ፡ ለኢየሱስ ፡ ይሁን
አየን ፡ አሸናፊነቱን
ኃያል ፡ እንደ ፡ እርሱ ፡ የለም
ይንገሥ ፡ ለዘለዓለም (፪x)

በደሙ ፡ ኃይል ፡ ጸደቅን ፡ በሥሙ ፡ ድል ፡ አገኘን
ማነው ፡ የሚቋቋመን ፡ ማንስ ፡ ነው ፡ የሚገታን
እንገሰግሳለን ፡ አሸናፊውን ፡ ይዘን
ወደ ፡ ቅድስቷ ፡ ሃገር ፡ በድል ፡ እንገባለን (፪x)

አዝ፦ ክብር ፡ ለኢየሱስ ፡ ይሁን
አየን ፡ አሸናፊነቱን
ኃያል ፡ እንደ ፡ እርሱ ፡ የለም
ይንገሥ ፡ ለዘለዓለም (፪x)

ክብር ፡ ምሥጋና ፡ ይዘን ፡ ከፊቱ ፡ እንቀርባለን
በዙፋኑ ፡ ላይ ፡ ላለ ፡ እንሰግድለታለን
ሁሉን ፡ የረታ ፡ ጌታ ፡ ንገሥ ፡ እንለዋለን
አቤት ፡ ለዘለዓለም ፡ እርሱ ፡ ኃያል ፡ ነው ፡ አሜን (፪x)

አዝ፦ ክብር ፡ ለኢየሱስ ፡ ይሁን
አየን ፡ አሸናፊነቱን
ኃያል ፡ እንደ ፡ እርሱ ፡ የለም
ይንገሥ ፡ ለዘለዓለም (፭x)