በወንጌል ፡ እውነት (Bewengiel Ewnet) - ተስፋዬ ፡ ጋቢሶ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ተስፋዬ ፡ ጋቢሶ
(Tesfaye Gabisso)

Lyrics.jpg


(10)

አዎን ፡ ይሆናል
(Awon Yehonal)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፬ (2012)
ቁጥር (Track):

(10)

ርዝመት (Len.): 5:02
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የተስፋዬ ፡ ጋቢሶ ፡ አልበሞች
(Albums by Tesfaye Gabisso)

አዝ፦ በወንጌል ፡ እውነት ፡ ወገቡን ፡ ታጥቆ
ስለ ፡ ሕይወት ፡ ቃል ፡ ጸንቶ ፡ ተዋድቆ
በጌታ ፡ ብርታት ፡ የከበበውን ፡ ጭፍራ ፡ ሰንጥቆ
በጐ ፡ ወታደር ፡ በድል ፡ አለፈ ፡ ያንን ፡ የሞትን ፡ ሸለቆ

ለተጨነቀ ፡ ልቡ ፡ እረፍት ፡ አግኝቶ
ጉዞውን ፡ ቢጀምር ፡ ወደ ፡ ሰማያዊ ፡ አገር ፡ አቅንቶ
ሰይጣን ፡ በተንኮል ፡ በወጥመዱ ፡ አጥሮ ፡ መንገድ ፡ ቢዘጋበት
ጌታም ፡ ይህን ፡ አይቶ ፡ ወጥመዱን ፡ ሰባብሮ ፡ በሩን ፡ ከፈተለት

አዝ፦ በወንጌል ፡ እውነት ፡ ወገቡን ፡ ታጥቆ
ስለ ፡ ሕይወት ፡ ቃል ፡ ጸንቶ ፡ ተዋድቆ
በጌታ ፡ ብርታት ፡ የከበበውን ፡ ጭፍራ ፡ ሰንጥቆ ፡
በጐ ፡ ወታደር ፡ በድል ፡ አለፈ ፡ ያንን ፡ የሞትን ፡ ሸለቆ

መዋጋትን ፡ እንዲለምድ ፡ ሸለቆ ፡ ወርዶ
ከቤት ፡ ከንብረቱ ፡ ከነፍሱ ፡ አብልጦ ፡ ጌታውን ፡ ወዶ
ሰልፉ ፡ በረታና ፡ ክፉኛ ፡ ተጠቅቶ ፡ እጅና ፡ እግሩ ፡ ዝሎ
ኢየሱስ ፡ ደርሶለት ፡ ድልን ፡ አወጀለት ፡ ባላንጣውን ፡ ጥሎ

አዝ፦ በወንጌል ፡ እውነት ፡ ወገቡን ፡ ታጥቆ
ስለ ፡ ሕይወት ፡ ቃል ፡ ጸንቶ ፡ ተዋድቆ
በጌታ ፡ ብርታት ፡ የከበበውን ፡ ጭፍራ ፡ ሰንጥቆ
በጐ ፡ ወታደር ፡ በድል ፡ አለፈ ፡ ያንን ፡ የሞትን ፡ ሸለቆ

እጆቹን ፡ በእርፉ ፡ ላይ ፡ አንዴ ፡ አሳርፏል
ወደኋላ ፡ ማየት ፡ ነውር ፡ በመሆኑ ፡ ሥራውን ፡ ቀጥሏል
እምነት ፡ ሳይጓደል ፡ አደራ ፡ ሳይበላሽ ፡ ተጠንቅቆ ፡ ታግሎ
እፎይ ፡ ማለቱ ፡ ነው ፡ በክብር ፡ ተራራ ፡ አክሊል ፡ ተቀብሎ

አዝ፦ በወንጌል ፡ እውነት ፡ ወገቡን ፡ ታጥቆ
ስለ ፡ ሕይወት ፡ ቃል ፡ ጸንቶ ፡ ተዋድቆ
በጌታ ፡ ብርታት ፡ የከበበውን ፡ ጭፍራ ፡ ሰንጥቆ
በጐ ፡ ወታደር ፡ በድል ፡ አለፈ ፡ ያንን ፡ የሞትን ፡ ሸለቆ (፪x)