በድንገት ፡ ይመጣል (Bedenget Yemetal) - ተስፋዬ ፡ ጋቢሶ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ተስፋዬ ፡ ጋቢሶ
(Tesfaye Gabisso)

Lyrics.jpg


(10)

አዎን ፡ ይሆናል
(Awon Yehonal)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፬ (2012)
ቁጥር (Track):

፲ ፪ (12)

ርዝመት (Len.): 6:42
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የተስፋዬ ፡ ጋቢሶ ፡ አልበሞች
(Albums by Tesfaye Gabisso)

የዓለም ፡ ፍጻሜ ፡ ምልክቶች
የጌታችን ፡ ቃሎች ፡ ትንቢቶቹ
ተፈፅመዋል ፡ የሚበዙቱ
የምጽአቱ ፡ ቀርቧል ፡ ሰዓቱ

አዝ፦ ጌታችን ፡ ኢየሱስ ፡ በታላቅ ፡ ግርማ ፡ በድንገት ፡ ይመጣል
በሰማይ ፡ ደመና ፡ ከቅዱሳኑ ፡ ጋር ፡ በክብር ፡ ይገለጣል
ፊቱ ፡ ልትቆም ፡ ምን ፡ ያህል (፪x) ፡ ተዘጋጅተሃል

ረሃብ ፡ ቸነፈሩ ፡ የምድር ፡ መናወጥ
የአህዛብ ፡ ዕውቀት ፡ መከራና ፡ ምጥ
ፍጥረቱን ፡ ይዞ ፡ ሲያንገዳግደው
የጨለማው ፡ ገዥ ፡ ጨንቆ ፡ ሲያብሰው

አዝ፦ ጌታችን ፡ ኢየሱስ ፡ በታላቅ ፡ ግርማ ፡ በድንገት ፡ ይመጣል
በሰማይ ፡ ደመና ፡ ከቅዱሳኑ ፡ ጋር ፡ በክብር ፡ ይገለጣል
ፊቱ ፡ ልትቆም ፡ ምን ፡ ያህል (፪x) ፡ ተዘጋጅተሃል

ሃሰት ፡ አሰራር ፡ ተዓምራቱ
የዓለም ፡ ሕዝቦችም ፡ ሲሳሳቱ
ዋጋ ፡ ሲያስከፍል ፡ ጌታን ፡ መጥራቱ
ቀኑም ፡ ቅርብ ፡ ነው ፡ የድል ፡ ንጋቱ

አዝ፦ ጌታችን ፡ ኢየሱስ ፡ በታላቅ ፡ ግርማ ፡ በድንገት ፡ ይመጣል
በሰማይ ፡ ደመና ፡ ከቅዱሳኑ ፡ ጋር ፡ በክብር ፡ ይገለጣል
ፊቱ ፡ ልትቆም ፡ ምን ፡ ያህል (፪x) ፡ ተዘጋጅተሃል

ፍፁም ፡ ባላሰብከው ፡ ሰዓት ፡ ይመጣል
ነቅቶ ፡ መጠበቁ ፡ ይሻልሃል
በምቾት ፡ ወጥመድ ፡ እንዳትታለል
በጸሎት ፡ እየተጋህ ፡ ተጠንቀቅ

አዝ፦ ጌታችን ፡ ኢየሱስ ፡ በታላቅ ፡ ግርማ ፡ በድንገት ፡ ይመጣል
በሰማይ ፡ ደመና ፡ ከቅዱሳኑ ፡ ጋር ፡ በክብር ፡ ይገለጣል
ፊቱ ፡ ልትቆም ፡ ምን ፡ ያህል (፪x) ፡ ተዘጋጅተሃል

ወንጌል ፡ ታውጆ ፡ የዘለዓለም
ሰዎች ፡ አምልጠው ፡ ከጥፋት ፡ ዓለም
የተባረከ ፡ ተስፋችን ፡ ኢየሱስ
ክፉን ፡ ደምስሶ ፡ በድል ፡ ሊነግስ

አዝ፦ ጌታችን ፡ ኢየሱስ ፡ በታላቅ ፡ ግርማ ፡ በድንገት ፡ ይመጣል
በሰማይ ፡ ደመና ፡ ከቅዱሳኑ ፡ ጋር ፡ በክብር ፡ ይገለጣል
ፊቱ ፡ ልትቆም ፡ ምን ፡ ያህል (፪x) ፡ ተዘጋጅተሃል