የልቤ ፡ አምላክ ፡ ሆይ (Yelebie Amlak Hoy) - ተስፋዬ ፡ ጋቢሶ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ተስፋዬ ፡ ጋቢሶ
(Tesfaye Gabisso)

Lyrics.jpg


(6)

አቤቱ ፡ መባረክን ፡ ባርከን
(Abietu Mebareken Barken)

ቁጥር (Track):

(1)

ርዝመት (Len.): 3:18
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የተስፋዬ ፡ ጋቢሶ ፡ አልበሞች
(Albums by Tesfaye Gabisso)

እግዚአብሔርን ፡ ይሄ ፡ ነው ፡ ተስፋ ፡ ያደረኩት
ታማኝነቱን ፡ አይቼ ፡ እጄን ፡ ልቤን ፡ የሰጠሁት
ያለ ፡ አዋቂዎች ፡ ልቦና ፡ በሰዎች ፡ ተስፋ ፡ ያደርጋል
ግን ፡ እግዚአብሔር ፡ ብቻ ፡ ድህንነትን ፡ ያዘጋጃል

አዝ፦ እጅግ ፡ ተቸግሬ ፡ ስማፀን ፡ አይተኸኝ
እኔ ፡ ከአንተ ፡ ጋር ፡ ነኝ ፡ አትፍራ ፡ እያልከኝ
በመጽናናት ፡ ሞልተህ ፡ ደስታን ፡ ታስታጥቀኛለህ
የልቤ ፡ አምላክ ፡ ሆይ ፡ የዘለዓለም ፡ ዕድል ፡ ፈንታዬ ፡ ነህ

የተማሰው ፡ ጉድጓድ ፡ አፉን ፡ በእኔ ፡ ላይ ፡ አልዘጋም
ጉልበቴ ፡ ባለቀ ፡ ጊዜ ፡ ለብቻዬ ፡ አልተውከኝም
ስለ ፡ ትንሿ ፡ እምነቴ ፡ ከባለጋራ ፡ ተሟግተህ
የድል ፡ አምባ ፡ አስረገጥከኝ ፡ ውጊያውን ፡ ሁሉ ፡ ፈጽመህ

አዝ፦ እጅግ ፡ ተቸግሬ ፡ ስማፀን ፡ አይተኸኝ
እኔ ፡ ከአንተ ፡ ጋር ፡ ነኝ ፡ አትፍራ ፡ እያልከኝ
በመጽናናት ፡ ሞልተህ ፡ ደስታን ፡ ታስታጥቀኛለህ
የልቤ ፡ አምላክ ፡ ሆይ ፡ የዘለዓለም ፡ ዕድል ፡ ፈንታዬ ፡ ነህ

ምሥጋናዬን ፡ እያዜምኩኝ ፡ በአንተ ፡ ደስ ፡ ይለኛል
በከንቱ ፡ በሚጠሉኝ ፡ ፊት ፡ ሞገስ ፡ አጐናጽፈኸኛል
ዓለም ፡ ብትሰርዘኝም ፡ የሕይወት ፡ መዝገብ ፡ አውቆኛል
እስከ ፡ መጨረሻው ፡ ድረስ ፡ ሕይወቴ ፡ በአንተ ፡ ይጸናል

አዝ፦ እጅግ ፡ ተቸግሬ ፡ ስማፀን ፡ አይተኸኝ
እኔ ፡ ከአንተ ፡ ጋር ፡ ነኝ ፡ አትፍራ ፡ እያልከኝ
በመጽናናት ፡ ሞልተህ ፡ ደስታን ፡ ታስታጥቀኛለህ
የልቤ ፡ አምላክ ፡ ሆይ ፡ የዘለዓለም ፡ ዕድል ፡ ፈንታዬ ፡ ነህ